Saturday, 10 October 2015 15:46

ፊልሞችን በዲጂታል መንገድ የሚያሰራጭ ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ፊልሞች ደህንነታቸው ተጠብቆ ለተመልካች ለማድረስ የሚያስችልና የፊልም ስርቆቶችን ያስቀራል የተባለ አዲስ ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ዋለ፡፡
አቢስውድ በተባለ ድርጅት ስራ ላይ የዋለው  አዲስ ቴክኖሎጂ፤ ፊልሞች በአንድ ጊዜ ከአንድ የማሰራጫ ስፍራ ወደተለያዩ ሲኒማ ቤቶች እንዲሰራጩ የሚያደርግና የፊልሙን ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ የሚጠብቅ ነው፡፡
 ድርጅቱ በፊልሞች ላይ የራሱን የይለፍ ኮድ በማድረግ ፊልሞች ያለ ባለቤቱ ፈቃድ እንዳይታዩ ቴክኖሎጂው ይከላከላል ተብሏል፡፡ድርጅቱ ከፊልም ስራዎች ተቀብሎ በየሲኒማ ቤቱ እንዲታዩ ለሚያደርጋቸው ሲኒማዎች ሁሉ ዋስትና የሚሰጥ ሲሆን ፊልሞቹ በምንም መንገድ ያለባለቤቱ ፈቃድ ለተመልካች ቢደርሱ ተጠያቂ የሚሆንበትን አሰራር ተግባራዊ የሚያደርግ ነው፡፡
 ድርጅቱ ፊልሞች በክልል ከተሞችም በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት እንዲታዩ ለማድረግ የሚችል ሲሆን በቀጣይ ከአገር ውጭ ፊልሞች የሚታዩበትን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ እንዳለው ተገልጿል፡፡

Read 1003 times