Saturday, 07 November 2015 10:03

የአልቃይዳው መሪ በምዕራባውያን ላይ ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ጥሪ አቀረቡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የአልቃይዳው መሪ አይማን አል ዛዋሪ፣ በመላው አለም የሚገኙ ጂሃዲስቶች በምዕራባውያን አገራት በተለይ ደግሞ በአሜሪካ ላይ ሌሎች ተጨማሪ የተናጠል የሽብር ጥቃቶችንት እንዲፈጽሙ ጥሪ ማቅረባቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡
አል ዛዋሪ በሳምንቱ መጀመሪያ በቪዲዮ ባስተላለፉትና በተለያዩ ድረገጾች በተሰራጨው የድምጽ መልዕክት፣ የቡድኑ አባላትና ደጋፊዎች በአሜሪካ ግዛት ውስጥ እንዲሁም ከአሜሪካ ጥቅም ጋር በሚተሳሰሩ በመላው አለም የሚገኙ ተቋማት ላይ በተናጠል ጥቃት እንዲፈጽሙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
16 ደቂቃ በሚፈጀው የቪዲዮ መልዕክታቸው፣ ፍልስጤማውያን ባለፈው ወር በእስራኤላውያን ላይ ያደረሱትን ጥቃት ያወደሱት የአልቃይዳው መሪ፣ አሜሪካ ለእስራኤል የምትሰጠውን ድጋፍ በመቀጠሏ ጂሃዲስቶች ዋነኛ የጥቃት ኢላማ ሊያደርጓት እንደሚገባ ገልጸው፣ “የእስራኤል ደጋፊ የሆኑ ሁሉ፣ በሞትና በኢኮኖሚ ድቀት ዋጋቸውን ማግኘት አለባቸው” ብለዋል፡፡  
የአልቃይዳው መሪ አይማን አል ዛዋሪ፣ ሶስት ሰዎች የሞቱበትንና 264 ያህልም የቆሰሉበትን የቦስተኑን ጥቃት ጨምሮ በተለያዩ የአለማችን አገራት ከዚህ ቀደም የተፈጸሙና በርካታ ሰዎችን ለህልፈተ ህይወት የዳረጉ በተናጠል የተፈጸሙ የሽብር ጥቃቶችን በዋቢነት በመጥቀስ፣ መሰል ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ለጂሃዲስቶች ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Read 1331 times