Saturday, 14 November 2015 10:03

“አፍሪካ ሰርከስ አርትስ ፌስቲቫል” ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   በአይነቱ የመጀመሪያው ነው የተባለውና ሰባት የአፍሪካ አገራት የሚካፈሉበት አፍሪካ ሰርከስ አርትስ ፌስቲቫል ከህዳር 17 እስከ 19 ቀን 2008 ዓ.ም በኦሮሞ ባህል ማዕከል ይካሄዳል፡፡
ፍካት ሰርከስ በሚያዘጋጀው በዚህ የሰርከት ፌስቲቫል ላይ ከግብፅ፣ ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣ ከማዳጋስካር፣ ከሴኔጋል፣ ከደበብ አፍሪካና ከዛምቢያ የተውጣጡና ስምንት ያህል በከፍተኛ ሁኔታ የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች በፌስቲቫሉ ላይ የሚሳተፉ ሲሆን ከ85 በላይ የሰርከስ ባለሙያዎች ካተታቸውን አዘጋጆቹ በጣይቱ ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡
በፌስቲቫሉ ላይ ከሰርከስ ትርኢቱ በተጨማሪ ከህዳር 21-22 ቀን 2008 ዓ.ም አውደ ርዕይ እና የልምድ ለውውጥ በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲዝ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

Read 2315 times