Saturday, 12 December 2015 11:07

ግብጽ በግድቡ ዙሪያ አለማቀፍ ሽምግልና ለመጠየቅ ጊዜው ገና ነው አለች

Written by 
Rate this item
(16 votes)

   የግብጽ የመስኖ ሚኒስትር ሆሳም ሞጋዚ ኢትዮጵያ በመገንባት ላይ ያለችውን አወዛጋቢውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ በተመለከተ  አለማቀፍ ሽምግልናን እንደአማራጭ ለመውሰድ ጊዜው ገና ነው ማለታቸውን አሃራም ኦንላይን የተባለው የአገሪቱ ድረገጽ ዘገበ፡፡
ግብጽ የግድቡ መሰራት ወደተፋሰሱ አገራት የሚደርሰውን የውሃ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሰዋል በሚል ስጋቷን ስትገልጽ እንደቆየች ያስታወሰው ዘገባው፣ በግድቡ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በአለማቀፍ ሸምጋዮች መፍታትን እንደአማራጭ እንደማትወስድና አፍሪካውያን አደራዳሪዎች በጉዳዩ ጣልቃ እንዲገቡ እንደማትፈልግ ሚኒስትሩ መናገራቸውን ገልጧል፡፡
ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኡመር አልበሽር ታላቁ ህዳሴ እውን መሆኑ ተረጋግጧል፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተባብረው ሊሰሩ ይገባል ሲሉ በተናገሩ ማግስት እንደሆነ የጠቆመው ዘገባው፣ ሚኒስትሩ በቅርቡም ግድቡ በታችኛው የተፋሰሱ አገራት ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ በተመለከተ የሚደረጉ የቴክኒክ ጥናቶች ሳይጠናቀቁ የግድቡ ግንባታ መፋጠኑ እንዳሳሰባቸው መናገራቸውን አስታውሷል፡፡
ሚድል ኢስት ሞኒተር በበኩሉ ከትናንት በስቲያ ባወጣው ዘገባ፣ ግብጽ የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስን በጉዳዩ ጣልቃ በመግባት በግድቡ ዙሪያ የሚታዩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ድጋፍ እንድታደርግ መጠየቋን አስነብቧል፡፡
የኢትዮጵያ፣ የግብጽና የሱዳን የውጭ ጉዳይና የመስኖ ሚኒስትሮች በግድቡ ዙሪያ በሚመክረው አስረኛው ዙር የጋራ ስብሰባ በሱዳን መዲና ካርቱም ከትናንት ጀምሮ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡

Read 5450 times