Tuesday, 29 December 2015 07:27

የጸሐፍት ጥግ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

(ስለ ህትመት)

• የመጀመሪያ መፃህፍቶቼን ሳሳትም የቀድሞው
ትውልድ ደራሲያን እየከሰሙ ነበር፡፡ ያኔ እኔም
አዲስ ደራሲ ስለነበርኩ ተቀባይነት አገኘሁ፡፡
ኦርሃን ፓሙክ
• በአንድ ጀንበር ስኬት ከመቀዳጀቴ በፊት 40
አመት ሞልቶኝ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ለ20 አመታት
ሳሳትም ቆይቻለሁ፡፡
ሜሪ ካር
• አንዳንድ ትላልቅ የአሜሪካ አሳታሚዎች አሁንም
የውጭ ፀሃፍት ሥራዎችን ይፈልጋሉ፡፡
ስቲፈን ኪንዘር
• ደራሲ ከመሆኔ በፊት በአሳታሚነት ዘርፍ ውስጥ
ሰርቻለሁ፡፡ እናም መፅሃፍ እንዴት እንደሚሰራ
አውቅ ነበር፡፡
ሎውረን ኦሊቨር
• ብዙ ፃፍ፤ ስለህትመቱ አታስብ - ስለ ፅሁፉ
ብቻ።
ጄፍሬይ ብራውን
• የመጀመሪያ ድርሰቴን 50 አመት ሲሆነኝ ዘግይቼ
ባሳትምም ከዚያን ጊዜ ወዲህ ስምንት ልብ
አንጠልጣይ ረዣዥም ልብ ወለዶችን ፅፌአለሁ።
ሃሊ ኢፍሮን
• እንዳልታተመ የፅሁፍ ክምር የሚሰነፍጥ ነገር
የለም፡፡
ሲልቭያ ፕላዝ
• መፃህፍቶቼን ከመታተማቸው በፊት ጮክ ብዬ
አንብቤአቸዋለሁ፡፡
ቤቨርሊ ክሊሪ
• ሰዎች የመፃፍ መብትን ከማሳተም መብት ጋር
እያምታቱት ያለ ይመስለኛል፡፡
ጆን ኮኖሊ
• እንግሊዝኛና ስፓኒሽኛ እናገራለሁ፡፡ በስፓኒሽኛ
እፅፋለሁ፤ መፃህፍቶቼ የሚታተሙት
በእንግሊዝኛ ነው፡፡
ኢሳቤል አሌንዴ
• አዲስ መፅሃፍ ሲታተም አንተ አሮጌውን
አንብብ።
ሳሙኤል ሮጀርስ
• ስራህ እ ስኪታተም ድ ረስ ፀ ሃፊ አ ይደለህም
የሚለው ሃሳብ ስህተት ነው፡፡
Andrew Vachss
• ምናልባት ለማሳተም አለመፈለግ ስለመፅሃፍ
እንዳስብ ብዙ ጊዜ ሳይሰጠኝ አይቀርም፡፡
ኬት አትኪንሰን
• በእርግጥ የመጀመሪያ ስምንት መፃህፍቶቼ
ታሪካዊ ልቦለዶች ነበሩ፤ ነገር ግን ጨርሶ
አልታተሙም፡፡
ካሮሊን ቢ.ኩኔይ

Read 1057 times