Saturday, 02 January 2016 11:56

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለመቄዶንያ የ200ሺብር ድጋፍ አደረገ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል ለሚያስገነባው ህንፃ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ200 ሺህ ብር ድጋፍ አደረገ፡፡
ባለፈው ማክሰኞ በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ባህረ ባደረጉት ንግግር፤ ባንካቸው የማዕከሉ ግንባታ ፕሮጀክት ፕሮፖዛል ተጠናቆ ሲቀርብ የበለጠ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቅሰው፣ በጉብኝቱ ወቅት በተመለከቱት ስሜታቸው በመነካቱ በግላቸው የ10ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አበርክተዋል፡፡
በመቄዶንያ ስም የዕርዳታ ቼኩን የተረከቡት የማዕከሉ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወ/ሪት ኤልሳቤጥ ንጉሤ፣ በአረጋውን ስም ምስጋና በማቅረብ ሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ባለሀብቶችና የግል ድርጅቶች ለማዕከሉ ግንባታ የኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
መቄዶንያ፣ መንግሥት ለማዕከሉ ልዩ ትኩረት በመስጠት በአዲስ አበባ ከተማ አያት ዋና መንገድ ላይ ከሊዝ ነፃ በሰጠው 30ሺህ ካ.ሜ ቦታ የአረጋውያን ማዕከል ለመገንባት እየተዘጋጀ ሲሆን ለማዕከሉ ግንባታ 300 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ አስታውቋል፡፡
መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን ማዕከል፤ በአሁኑ ወቅት ከ850 የሚበልጡ አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን እየተንከባከበ ሲሆን የተረጂዎቹን ቁጥር 3ሺ ለማድረስ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡


Read 1656 times