Saturday, 23 January 2016 13:43

ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቤል ተስፋዬ ለኦስካር ታጨ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ትውልደ ኢትዮጵያዊው የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ አቤል ተስፋዬ /ዘ ዊኪንድ/፤ “ኧርንድ ኢት” በተባለው የፊልም ማጀቢያ ሙዚቃው፣ለዘንድሮው የኦስካር ሽልማት መታጨቱ ተዘገበ፡፡

“ፊፍቲ ሼድስ ኦፍ ግሬይ” ለተባለው ፊልም በማጀቢያ ሙዚቃነት የተሰራው “ኧርንድ ኢት”፣ በኦስካር ሽልማት የምርጥ ወጥ ሙዚቃ ዘርፍ መታጨቱን ዘ ካናዲያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡

በዘርፉ ለሽልማት ከታጩት አምስት ሙዚቃዎች መካከል በታዋቂዋ ድምጻዊት ሌዲ ጋጋ የተቀነቀነውና “ዘ ሃንቲንግ ግራውንድ” ለተባለው ፊልም በማጀቢያነት የተሰራው “ቲል ኢት ሃፕንስ ቱ ዩ” ይገኝበታል፡፡  
የዘንድሮው የኦስካር ሽልማት ስነስርዓት በመጪው የካቲት መጨረሻ እንደሚካሄድና የመድረክ መሪውም ታዋቂው የሆሊውድ ተዋናይ ክሪስ ሮክ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን በኤቢሲ ቴሌቪዥን በቀጥታ ይተላለፋል ተብሏል፡፡

Read 3535 times