ትውልደ ኢትዮጵያዊው የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ አቤል ተስፋዬ /ዘ ዊኪንድ/፤ “ኧርንድ ኢት” በተባለው የፊልም ማጀቢያ ሙዚቃው፣ለዘንድሮው የኦስካር ሽልማት መታጨቱ ተዘገበ፡፡
“ፊፍቲ ሼድስ ኦፍ ግሬይ” ለተባለው ፊልም በማጀቢያ ሙዚቃነት የተሰራው “ኧርንድ ኢት”፣ በኦስካር ሽልማት የምርጥ ወጥ ሙዚቃ ዘርፍ መታጨቱን ዘ ካናዲያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡
በዘርፉ ለሽልማት ከታጩት አምስት ሙዚቃዎች መካከል በታዋቂዋ ድምጻዊት ሌዲ ጋጋ የተቀነቀነውና “ዘ ሃንቲንግ ግራውንድ” ለተባለው ፊልም በማጀቢያነት የተሰራው “ቲል ኢት ሃፕንስ ቱ ዩ” ይገኝበታል፡፡
የዘንድሮው የኦስካር ሽልማት ስነስርዓት በመጪው የካቲት መጨረሻ እንደሚካሄድና የመድረክ መሪውም ታዋቂው የሆሊውድ ተዋናይ ክሪስ ሮክ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን በኤቢሲ ቴሌቪዥን በቀጥታ ይተላለፋል ተብሏል፡፡
Published in
ጥበብ