Saturday, 30 January 2016 12:46

“ድብቁ የሸካ ዳን ውበት” ዘጋቢ ፊልም ትላንት ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   በሸካ አካባቢ የሚኖሩ ብሔር ብሄረሰቦችን ባህላዊ ትውፊትና የአካባቢውን ተፈጥሮአዊ ውበት የሚያሳየውና የ22 ደቂቃ ርዝመት ያለው “ድብቁ የሸካ ደን ውበት” ዘጋቢ ፊልም ትላንት ምሽት በልዑል ሲኒማ ተመረቀ፡፡ የሸካ ዞን አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፣ መልካ ኢትዮጵያና የአውሮፓ ህብረት ሲቪል ሶሳይቲ ፈንድ በመተባበር የሰሩትን ይህን ፊልም፤ አርቲስት ዮሃንስ ፈለቀ ያዘጋጀው ሲሆን በብሉ ሚዲያ ፊልም ፕሮዳክሽን ተሰርቶ ቀርቧል፡፡ በምርቃቱ ላይ የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች፣ የሸካ ዞን ኃላፊዎች፣ የመልካ ኢትዮጵያ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ጋዜጠኞች ተገኝተዋል፡፡

Read 2124 times