Saturday, 13 February 2016 12:08

የሰሜን ኮርያ የጦር ሃይል አዛዥ በፕሬዚዳንቱ ትዕዛዝ ተገድለዋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

  - በሙስና ተጠርጥረዋል ቢባልም፣ በስነ-ምግባራቸው እንደሚታወቁ ተነግሯል
           - ፕሬዚዳንቱ በቅርቡ የመከላከያ ሚኒስትሩን በሞርታር አስገድለዋል
    የሰሜን ኮርያ የጦር ሃይል አዛዥ ጄኔራል ሪ ያንግ ጊል፤ በሙስናና የግል ጥቅምን በማካበት ህገወጥ ተግባር ተሰማርተው ተገኝተዋል በሚል ባለፈው ሳምንት በአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ትዕዛዝ መገደላቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደገለጹ ስካይ ኒውስ ዘገበ፡፡
ላለፉት ሶስት አመታት የአገሪቱ የጦር ሃይል አዛዥ ሆነው ያገለገሉት ጄኔራል ሪ ያንግ ጊል ለስነ-ምግባር መርሆዎች ተገዢ መሆናቸው የተመሰከረላቸው ግለሰብ ናቸው ያለው ዘገባው፣ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ጄኔራሉን ያለአግባብ የወነጀሉት ለግድያው ሰበብ ለመፈለግ ነው መባሉን ፀቁሟል፡፡ ግድያውን በተመለከተ ተጨባጭ ማረጋገጫ ባይገኝም፣ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ከወራት በፊት የቀድሞውን የአገሪቱ  የመከላከያ ሚኒስትር በሞርታር ማስገደላቸው ይህንን ግድያም ሊያስፈጽሙት እንደሚችሉ ያመላክታል መባሉን ዘገባው ገልጧል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በቅርቡ የፓርቲ መሪዎችን በቁልፍ የአገሪቱ ጦር ሃይል የስልጣን ቦታዎች ላይ መሾማቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ይህም በጄኔራሉ ላይ ተፈጸመ ከተባለው ግድያ ጋር ሊያያዝ እንደሚችልና አዲሶቹ ባለስልጣናትም በጄኔራሉ ግድያ ውስጥ እጃቸው ሊኖርበት ይችላል መባሉንም አብራርቷል፡፡

Read 2458 times