Saturday, 27 February 2016 12:10

ደራሲያን ማህበር ደራሲ ይልማ ኅብተየስን ዛሬ ይዘክራል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በወንጀልነክ የፈጠራ ስራዎቻቸው የሚታወቁትን እና 17 መፅሀፍትን
ለንባብ ያበቁትን አንጋፋ ደራሲ ይልማ ኀብተየስን ዛሬ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በቅርስ ጥናትና ጥበቃ አዳራሽ እንደሚዘክር አስታወቀ፡፡ በዕለቱም በቅርቡ ለህትመት የበቃው “የቤቱ መዘዝ” የተሰኘው የደራሲው 17ኛ መፅሀፍ እንደሚመረቅም ታውቋል፡፡ የ78 ዓመቱ ደራሲ ይልማ ሃብተየስ በ1958 ዓ.ም “እሱን ተይው” የተሰኘ የመጀመሪያ የወንጀል ምርመራ የፈጠራ ፅሁፋቸው
ያሳተሙ ሲሆን ከዚያ በፊት “ያልታደለች በሰው ሰርግ ተዳረች” የተባለ ልብ ወለድ ማሳተማቸውም ታውቋል፡፡ ደራሲው “ሶስተኛ ሰው”፣ “ከቀብር መልስ”፣ “ያልተከፈለ ዕዳ”፣ “ሳይናገር ሞተ”፣ “ደስ ያለው ሀዘንተኛ”፣ “ያበቅ የለሽ ኑዛዜ” እና ሌሎችንም የወንጀል ምርመራ ፈጠራ
መፅሀፍትን ለንባብ አብቅተዋል፡፡ በዝክር ፕሮግራሙ ላይ በደራሲው ስራዎች፣ በህይወታቸውና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት የሚካሄድ ሲሆን የደራሲያን ማህበር ለአንጋፋው ደራሲ እውቅና እንደሚሰጣቸውም ተገልጿል፡

Read 1760 times