Saturday, 27 February 2016 12:12

የአድዋ ድልን የተመለከተ የኪነ-ጥበብ ዝግጅት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

120ኛውን የአድዋ ድል በዓል በማስመልከት “ሞሰብ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን” የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡30ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ኪነ-ጥበባዊ ዝግጅቶችንያካሂዳል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የአዝማሪ ሙዚቃ፣ዲስኩር፣ ወግ፣ ሽለላና ፉከራ እንዲሁም በባህላዊ ሙዚቃ የታጀበ ግጥም የሚቀርብ ሲሆን የመድረክ ላይ ቀጥታ ስዕልም ለታዳሚዎች እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ ሞሰብ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን የተለያዩ ባህላዊና አገራዊ ዝግጅቶችን በማድመቅ እንደሚታወቅየቡድኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጣሰው ወንድምተናግረዋል፡፡

Read 1125 times