በደራሲና ዳይሬክተር ረዲ በረካ ተፅፎ የተዘጋጀውና በስፖትስ ፊልም ፕሮዲዩስ ተደርጎ የቀረበው “50 ሎሚ” ፊልም፤ ከነገ በስቲያ ሰኞ በብሄራዊ ቴአትር ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በቀይ ምንጣፍ ስነ-ስርአት ይመረቃል፡፡ በማህበረሰቡ የተገፋ አንድ ታዳጊ የኑሮ ትርጉም ሳይገባው በወንጀል ተዘፍቆና በፍቅር ተይዞ የሚዋትትበትን ሂደት የሚተርከውን ይህን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ስድስት ወራትን የፈጀ ሲሆን ተዘራ ለማ፣ የትናየት ታምራት (ሚሚ) ፋሪስብሩ፣ ሱራፌል ፀጋዬና ሌሎች አንጋፋና ወጣት ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡
Saturday, 27 February 2016 12:17
“50 ሎሚ” ፊልም ከነገ በስቲያ ይመረቃል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና