Saturday, 05 March 2016 11:23

“መፃሕፍት ለሁሉም ቤት” ኤግዚቢሽን ዛሬና ነገ ይቀርባል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

“መጻሕፍት ለሁሉም ቤት” በሚል የመጻሕፍት መደብር ባለቤቶች በጋራ የሚያዘጋጁት ሁለተኛው የመጻሕፍት ኤግዚቢሽን ዛሬና ነገ ጥቁር አንበሳ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው ትራኮን ታወር አንደኛ ፎቅ ላይ እንደሚቀርብ የ `እነሆ` መጻሕፍት መደብር ባለቤት አቶ ኤርሚያስ በላይነህ ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡ ኤግዚቢሽኑ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን የተሳታፊዎች ቁጥር ከመጀመሪያው አውደ ርዕይ እንደጨመረ ታውቋል፡፡
ተሳታፊዎቹ “እነሆ መጻሕፍት”፣ ክብሩ መጻሐፍት፣ “ሊት-ማን መጻሐፍት፣ Book light፣ ኤዞፕ መጻሕፍት” እና ሌሎች ሲሆኑ በኤግዚቢሽኑ ላይ የታሪክ፣ ፍልስፍና፣ የልቦለድ፣ የተረቶች…እንዲሁም እምብዛም ገበያ ላይ የማይገኙ የቆዩ መጻሕፍት ይቀርባሉ ተብሏል፡፡

Read 1095 times