ዓመታዊ ትርፉን 10ቢ. ዶላር ለማድረስ አቅዷል
በትርፋማነቱ ከአፍሪካ አየር መንገዶች መሪነቱን የያዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ በፈረንጆች የ2014-15 አመት የ3.53 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱንና ትርፉ ከቀደመው አመት የ12 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን “ብሉምበርግ” ዘገበ፡፡
ምንም እንኳን አመቱ ለአፍሪካ አየር መንገዶች ፈታኝ የነበረ ቢሆንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን፣ ፈተናዎችን በመጋፈጥ፣ ወጪዎቹንና የሽያጭ አገልግሎቶቹን በማስፋፋትና አሰራሮቹን በማሻሻል በትርፋማነቱ መቀጠሉን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም መናገራቸውን ዘገባው ገልጿል፡፡
አየር መንገዱ ከ2.1 ቢሊዮን ዶላር በላይ በመመደብ፣ 20 ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላኖችን ለመግዛት ማዘዙንና በመጪዎቹ አስር አመታት ጊዜ ውስጥ አመታዊ ትርፉን 10 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ አቅዶ እየታተረ እንደሚገኝም ዘገባው አስታውሷል፡፡
Published in
ዜና