Saturday, 19 March 2016 10:56

“ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል” በግልገል ጊቤ 3 ጉዳይ ሳሊኒን ከሰሰ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ግንባታው ግማሽ ሚሊዮን ሰዎችን ለርሃብ አጋልጧል ብሏል
   አለማቀፉ የመብት ተሟጋች ተቋም “ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል” የጣሊያኑ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኩባንያ በገነባው የግልገል ጊቤ 3 የሃይል ማመንጫ ግድብ ሳቢያ በኢትዮጵያና በኬንያ የሚኖሩ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህልውና ለከፋ አደጋ አጋልጧል በሚል የኢኮኖሚ ትብብርና ልማት ድርጅት ለተባለው ተቋም መክሰሱን አስታወቀ፡፡
ኩባንያው በገነባው በዚህ ግድብ ሳቢያ ግማሽ ሚሊዮን ያህል ሰዎች ለርሃብ አደጋ ተጋልጠዋል ያለው ተቋሙ፤ በኢትዮጵያና በኬንያ ለሚኖሩ መቶ ሺህ ያህል ሰዎች የህልውና መሰረት የሆነውን የኦሞ ወንዝ ነባር ፍሰት አቅጣጫ ማስቀየሩ፣ በሰዎቹ ህልውና ላይ በቀጣይ ከፍተኛ አደጋ ይፈጥራል ሲል ተቋሙን ከስሷል፡፡
ሳሊኒ በአካባቢው የሚኖሩ ዜጎችን ይሁንታ ሳያገኝ ግድቡን ገንብቷል ያለው ተቋሙ፣ ምንም እንኳን በግንባታው ሳቢያ በነዋሪዎቹ  ላይ ለሚደርሰው ጥፋት ካሳ ለመስጠት ቃል ቢገባም፣ የገባውን ቃል አላከበረም ሲል አቤቱታውን አሰምቷል፡፡
የ “ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል” ዳይሬክተር ስቴፈን ኮሪ፣ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን የግድቡ ግንባታ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ በተመለከተ የቀረበለትን ማስረጃ ችላ ብሏል፤ የገባውን ቃል አላከበረም፣ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን መብት ጥሷል ብለዋል፡፡

Read 3465 times