Saturday, 26 March 2016 12:04

የአፍሪካ አገራት የደስተኛነት ደረጃ ወጣ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

 ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ትሻላለች ተብሏል
    ሰስቴኔብል ዴቨሎፕመንት ሶሊዩሽንስ ኔትዎርክ የተባለ ተቋም በአፍሪካ አህጉር በደስተኝነት ቀዳሚ ናቸው ያላቸውን አገራት ዝርዝር ይፋ ማድረጉን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት፣ የማህበራዊ ድጋፍ፣ አማካይ ዕድሜ፣ ለሙስና ያለውን አመለካከትና የመሳሰሉትን መስፈርቶች በመጠቀም አገራቱን በደረጃ ያስቀመጠው የተቋሙ ሪፖርት፤አልጀሪያን ከአፍሪካ እጅግ ደስተኛዋ አገር በማለት በቀዳሚነት አስቀምጧታል። ሞሪሽየስና ሊቢያ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን የያዙ ሲሆን ሶማሊያ፣ ቱኒዝያ፣ ናይጀሪያ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በቅደም ተከተል እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ከአለማችን አገራት በደስተኛነት የመጨረሻውን ደረጃ ከያዙት አስር አገራት መካከል ስምንቱ አፍሪካውያን ናቸው ያለው ዘገባው፣ እነሱም ማዳጋስካር፣ ታንዛኒያ፣ ላይቤሪያ፣ ጊኒ፣ ሩዋንዳ፣ ቤኒን፣ ቶጎ እና ብሩንዲ መሆናቸውን ጠቁሟል፡፡
ተቋሙ በአለማቀፍ ደረጃ ባደረገው የአገራት የደስተኝነት ሁኔታ ጥናት፣ የመጀመሪያዎቹን 100 ደረጃዎች ከያዙት አገራት መካከል መካተት የቻሉት የአፍሪካ አገራት አምስት ብቻ መሆናቸውንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2765 times