Monday, 04 April 2016 07:28

የሠማያዊ ፓርቲ አመራሮች እገዳ ተሻረ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ሊቀመንበሩን ጨምሮ አምስት የሠማያዊ ፓርቲ አመራሮች እንዲባረሩና እንዲታገዱ በስነስርአት ኮሚቴ የተላለፈውን ውሣኔ የፓርቲው ኦዲትና ኢንስፔክሽን ውድቅ አድርጐታል፡፡
የስነስርአት ኮሚቴው በምርጫ 2007 አምስት አመራሮች ያለአግባብ የፓርቲውን ገንዘብ አባክነዋል በሚል የቀረበለትን ክስ ሲመረምር ቆይቶ ባሳለፍነው ሣምንት ውሣኔ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን በውሣኔውም የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነትና የሂሣብ ክፍል ሃላፊው አቶ ወረታው ዋሴ ከፓርቲው ሙሉ ለሙሉ እንዲባረሩ፤ የፓርቲው ም/ሊ/መንበር የነበሩት አቶ ስለሺ ፈይሳና የምክር ቤት አባልዋ ወ/ት ወይንሸት ሞላ፣ ለሁለት አመት እንዲታገዱ እንዲሁም አቶ ጌታነህ ባልቻ ለሶስት ወር እንዲታገዱ ያሳለፈውን ውሣኔ፣ የፓርቲው ኦዲትና ኢንስፔክሽን “አግባብ አይደለም” በማለት ሽሮታል፡፡
ለተከሳሾቹ ከመገለፁ በፊት በማህበረሰባዊ ሚዲያዎች ውሳኔው ይፋ መሆኑ አግባብ አለመሆኑን የጠቀሰው የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴው፤ ውሳኔውም የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ ያልተከተለና የስነ ስርዓት ቅጣት አላማን ያላገናዘበ ነው ብሏል፡፡
መባረራቸውና መታገዳቸው ተገልፆ የነበረው የፓርቲው አመራሮች፤ መደበኛ ስራቸውን እንዲቀጥሉ የወሰነው  የኦዲትና ኢንስፔክሽን ኮሚቴው፤ በማህበራዊ ድረ ገፆች ይሄን አስመልክቶ የሚካሄዱ ዘመቻዎች መቆም እንዳለባቸውም አሳስቧል፡፡

Read 2993 times