Monday, 04 April 2016 08:12

አምበልነት ደስ ቢልም ከባድ ሃላፊነት ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የተጨዋቾችስነልቦና ጠንካራእንዲሆን ስራዎች ያስፈልጋሉ፡፡ ዋና አምበል ሽመልስ በቀለ
        ከአልጄርያ ጋር በተደረጉት ሁለት የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ዋልያዎቹ ያሳዩትአቋም የተለያየ ለምን ሆነ?
የመጀመርያው ጨዋታ ላይ ያው ተደጋግሞ እንደተገለፀው እኛ በተለያዩ ውጫዊ ምክንያቶች ድካም ነበረብን፡፡ እነሱም በሜዳቸው እንደመጫወታቸው ጫና ፈጥረው ብልጫ ወስደውብናል፡፡ እንደምታውቀው በዋልያዎቹ ስብስብ ብዙ አዳዲስ ተጨዋቾች አሉ፡፡ እነሱ በወጡበት ጊዜ የተፈጠሩ የተለያዩ ችግሮች አዲስ እንደመሆናቸው ፈተና ውስጥ ከቷቸዋል፡፡  የተፈጠሩ ውጫዊ ተፅእኖዎች በአካል ብቃትም በስነልቦናም ለመቋቋም ባለመቻላቸው በመጀመርያው ጨዋታ ያ ከባዱ ሽንፈት መጋፈጥ ግድ ሆኖብናል፡፡
ዋናው ችግር በትራንስፖርት የተፈጠረውን አድካሚ ጉዞ እና መጉላላት ነው፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ለሚደረግ ጨዋታ 38 ሰዓታት በትራንዚት መጓጓዝ በጣም ይከብዳል፡፡ ረቁቅ ጉዞ ስታደርግ በፌደሬሽኑ በኩል ቀደም ብሎ መዘጋጀት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ከነበረው ድካም አንፃር በጨዋታ መልካም ብቃት ማሳየት አይቻልም፡፡ ስፖርተኛ በቂ እረፍት እና ሙሉ አቅም ግንባታ ያስፈልገዋል፡፡
የአልጄርያው አሰልጣኝ ዮሃን ጉርኩፍ በመልሱ ጨዋታ የአንተን ብቃት ተመልከተው ምርጡ ተጨዋች እንደሆንክ እና ረጅም ጊዜ ሲከታተሉህ እንደነበር ተናግረዋል የሰሜን አፍሪካልምድ እንዳለህ ይታወቃል በፊት በሊቢያ ክለብ ትጫወት ነበር፤ አሁን ደግሞ ግብፅ ነው ያለሀው፡፡ የአልጄርያ ክለቦች ፍላጎት ያላቸው ይመስለኛል?
ከተወሰኑ ዓመታት በፊት አንድ የአልጄርያ ክለብ በጥሩ የዝውውር ሂሳብ እያነጋገረኝ ነበር፡፡ በአጋጣሚ አልተሳካም ፤ አሁን ደግሞ የአልጄርያ ፌደሬሽን ክለቦች ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች የሚገዙበትን ሁኔታ በመዝጋቱ እድል ያለ አይመስለኝም፡፡ የግብፅ ሊግን ጉርኩፍ የሚከታተል ይመስለኛል፡፡ አስተያየቱም በዚያ ላይ የተንተራሰ ነው፡፡
ብሄራዊ ቡድኑ በቀጣይ በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የማለፍ ዕድል ይኖረዋል?
በእኔበኩል እድል አለን ብዬ ነው የማስበው፤፤ ቀሪዎቹን ሁለት ጨዋታዎች ካሸነፍን 11ነጥብ ይኖረናል፡፡ ይሄ 11 ነጥብ ደግሞ በጥሩ ሁለተኛ ለማለፍ ያስችለናል ብዬ ነው የማስበው። በየምድቡ ያሉት መሪዎቹ እንኳን 7 ነጥብ ነው ያላቸው በዚህ ስሌት መሰረት የኢትዮጵያ ዕድል የሚወሰን ይሆናል፡፡
በወዳጅነት ጨዋታ የተጠናከረ ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል፤ ተጨዋቾችን በደህና ሆቴል ማሳረፍ ብቻ አይደለም፤ በስነልቦና በቂ ዝግጅት እንዲኖራቸው ማድረግና መንከባከብ ያስፈልጋል፡፡ ሞራል የሚጠብቁ ተግባራት በፌደሬሽኑ መከናወን አለባቸው፡፡ የቡድኑ ተጨዋቾች ጭንቅላታቸው ጠንካራ እንዲሆን የሚያግዙ አሰራሮች ያስፈልጋሉ
የብሄራዊ ቡድኑ አምበል ስትሆን ለመጀመርያ ጊዜ ነው የምታስተላልፈው መልዕክት ምንድነው?
እውነቱን ለመናገር በመልሱ ጨዋየታ ያሉብንን ችግሮች ተቋቁመን ህዝብ ለማስደሰት መስዕዋትነት ከፍለናል፡፡ ህዝቡ ይሄን እንዲረዳው እፈልጋለሁ፣፣ በሌላ በኩል 7ለ1 በመሸነፋችን እኛም አዝነናል፤ በቡድኑ ስምም ይቅርታም መጠየቅ እፈልጋለሁ፡፡ የብሄራዊ ቡድን ዋና አምበልነት የሚያስደስት ግን ከባድ ሃላፊነት ነው፡፡ ቡድንህ ጥሩ ውጤት እንዲያመጣ ማነሳሳቱ፤ ከተጨዋቾች ጋር ተመካክሮ መስራቱ፤ ሃላፊነቱ መውሰዱ የሚያስደስት ነው፡፡ እናም ባለኝ አቅም አገሬን እያገዝኩ ውጤታማ እያደረግኩ መቀጠል እፈልጋለሁ፡፡

Read 1124 times