በገጣሚና ጋዜጠኛ አንዱአለም ጌታቸው የተፃፈው “ዮሪካ” የተሰኘ የግጥም መድበል ዛሬ ከ3 ሰአት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴያትር ቤት ይመረቃል፡፡ የጋዜጠኛው የበኩር ስራ የሆነው የግጥም ስብስቡ በማህበራዊ፣ በፍቅርና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያጠነጥናል ተብሏል። የግጥም መጽሐፉ መጠሪያ የሆነውን “ዮሪኮ”ን ጨምሮ 50 ግጥሞችን በ64 ገፆች ያካተተው መድበሉ፤ በ30 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
በተለያዩ ጋዜጦችና መጽሔቶች ላይ በሪፖርተርነት ያገለገለው ገጣሚው፤ በአሁኑ ወቅት በዛሚ ኤፍ ኤም የሚቀርበው “ጥበብ ለሁሉም” የተሰኘው ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ ነው፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና