Monday, 04 April 2016 08:47

“ድርጅታዊ የጤና ምርመራ” መጽሐፍ ተመረቀ”

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኮሎኔል በፈቃደ ገብረየስ የተዘጋጀው “ድርጅታዊ የጤና ምርመራ” የተሰኘው መጽሐፍ በትላንትናው እለት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ተመርቋል። ማንኛውም ድርጅት አመታዊ የጤና ምርመራ ማድረግ እንደሚገባው የሚገልፀው መጽሐፉ፤ የጤና ምርመራ ማድረግ ጠንካራ የሆነ ድርጅትን ለመፍጠር እንደሚረዳ ያስረዳል፡፡
በ153 ገፆች የተቀነበበው መፅሃፉ፤ በ100 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ባለፉት ሰላሳ አመታት በተለያዩ የውትድርና ዘርፎች ያገለገሉት ኮሎኔል ፈቃደ፤ በውትድርና ሳይንስና በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ሁለት የማስተርስ ዲግሪ እንዳላቸው ታውቋል፡፡ ደራሲው ከሁለት ወራት በፊት “ስትራቴጂ” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃታቸው ይታወሳል፡፡

Read 892 times