Saturday, 09 April 2016 10:20

ሰሜን ኮርያ ከቻይና የንግድ ማዕቀብ ተጣለባት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   ቻይና ባለፈው ወር በተመድ ማዕቀብ ከተጣለባት ሰሜን ኮርያ ጋር ስታከናውነው የቆየቺውን የተለያዩ የውድ ማዕድናት ምርቶች ግዢና የነዳጅ ሽያጭ ለማቋረጥ የሚያስችሉ የተለያዩ የንግድ ማዕቀቦችን መጣሏን አስታወቀች፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው፤ሰሜን ኮርያ የውጭ ንግድ ምርቶች ሁለት ሶስተኛውን ያህል በመግዛት የምትታወቀው ቻይና፣ የሰሜን ኮርያ ዋነኛ የወጪ ንግድ ምርቶች የሆኑትን ወርቅና ሌሎች ውድ ማዕድናት ላለመግዛት ወስናለች፡፡ የቻይና መንግስት ከሰሜን ኮርያ የግዢ ማዕቀብ ከጣለባቸው ምርቶች መካከል ብረት፣ ወርቅ ቲታኒየም እንደሚገኙበት የጠቆመው ዘገባው፣ ሰሜን ኮርያ በ2013 ለውጭ ገበያ ካቀረበቺው ምርት 65 በመቶ የሚሆነውን የገዛቺው ቻይና እንደሆነች አስታውሷል፡፡
ቻይና ከዚህ በተጨማሪም ለሰሜን ኮርያ የአውሮፕላን ነዳጅ መሸጥ እንደማይቻል ከሰሞኑ ባወጣቺው ማዕቀብ ወስናለች ያለው ዘገባው፣ ማዕቀቡ በሰሜን ኮርያ የወጪ ንግድ ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ ይፈጥራል መባሉን ገልጧል፡፡
ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማና የቻይናው አቻቸው ዢ ጂፒንግ ባለፈው ሳምንት ዋሽንግተን ውስጥ በተካሄደው አለማቀፉ የኒውክሌር ደህንነት ጉባኤ ላይ ተገናኝተው በሰሜን ኮርያ የኒውክሌር እንቅስቃሴ ላይ ቻና ለመፍጠር መስማማታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ አሜሪካ ቻይና በሰሜን ኮርያ ላይ የጣለቺውን የንግድ ማዕቀብ በደስታ እንደተቀበለቺውም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1516 times