እናት የማስታወቂያ ስራ ከጀርመን የባህል ማዕከልቀሐ ከብሄራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ - መፃህፍት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር በሚያዘጋጁት “ጎተ ወርሀዊ የመፅሀፍ ውይይት መድረክ”፤ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ -
መዛግብትና ቤተ - መፃህፍት ኤጀንሲ አዳራሽ“የኔ ቢጤ ሰማይ” በተሰኘው የገጣሚ መስፍንወንደሰን የግጥም መድበል ላይ ውይይት ያካሂዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት ሃያሲና ገጣሚ ደረጀ በላይነህ ሲሆኑ ፍላጎት ያለው
ማንኛውም ሰው በውይይቱ ላይ ይሳተፍ ዘንድ አዘጋጆቹ ጋብዘዋል፡፡
Saturday, 07 May 2016 13:08
“የኔ ቢጤ ሰማይ” ነገ ውይይት ይደረግበታል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና