Saturday, 14 May 2016 13:28

የፀደንያ “የፍቅር ግርማ” ለአድማጭ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

“ገዴ” እና “ቢሰጠኝ” በተሰኙ ቀደምት አልበሞቿ ተቀባይነትን ያገኘችው ዝነኛዋ ድምፃዊት ፀደንያ ገ/ማርቆስ፤ “የፍቅር ግርማ” የተሰኘ ሶስተኛ አዲስ አልበሟ ለአድማጭ ቀረበ፡፡ አልበሙ 11 ዘፈኖችን ያካተተ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ አንዱ የተፈራ ደምሴ ግጥም የሆነው “ካምፕፋየር” የተሰኘ የእንግሊዝኛ ሙዚቃ እንደሆነ ድምፃዊቷ ለአዲስ አድማስ ገልፃለች፡፡ የአምስቱን ዘፈኖቿን ግጥም አንጋፋው ገጣሚ ይልማ ገ/አብ፣ አንዱን ገጣሚና ፀሐፌ ተውኔት ጌትነት እንየው፣ ሶስቱን ፋሲል ከበደ የተሰኘ አዲስ ገጣሚ፣አንዱን ደግሞ #ህመሜ” የተሰኘው ነጠላ ዜማዋ ገጣሚ አብዲ ራዋ የሰሩላት ሲሆን ዜማውን በአብዛኛው ራሷ ድምፃዊቷ እንደሰራችና አንዱን ሄኖክ መሀሪ እንደሰራላት ተናግራለች፡፡
“ካምፕፋየር” የተሰኘውን የእንግሊዝኛ ሙዚቃ ቅንብር ኬሊ አለን የሰራላት ሲሆን  የሌሎቹን ቅንብር አቤል ጳውሎስ መስራቱንና አሳትሞ ያከፋፈለው ኤራ ኮሙዩኒኬሽንና ኤቨንት እንደሆነ ድምጻዊቷ ጠቁማለች፡፡  
 ጸደንያ በዘንድሮ ዓመት ብቻ የ“አፍሪካ ሚዩዚክ አዋርድ” (አፍሪማ)፣ የ“ለዛ አድማጮች” እና ለ“ሀሪየት” ፊልም በሰራችው የማጀቢያ ሙዚቃ የ#ጉማ አዋርድ” ሶስት ሽልማቶችን አሸናፊ ለመሆን የበቃች ሲሆን በአገራችን ብቸኛዋ የ“ኮራ አዋርድ” ተሸላሚ እንደሆነችም ይታወቃል፡፡


Read 1809 times