Saturday, 14 May 2016 14:04

“አዲስ ኮንሰርት” ሳምንት ቅዳሜ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

አንጋፋው ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህና “ዘመናይ ማርዬ” በተሰኘው አልበሙ የሚታወቀው
ልጅ ሚካኤል የሚያቀነቅኑበት “አዲስ ኮንሰርት” የዛሬ ሳምንት ከሚሊኒየም አዳራሽ ጀርባ በሚገኘው ፋና ፓርክ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ የጆርካ ኤቨንት ኦርጋናይዘር ማርኬቲንግ ማናጀር አቶ ታደሰ ታምራት አስታወቁ፡፡ ከሚካኤል በላይነህና ከልጅ ሚካኤል በተጨማሪ ያሬድ ነጉ (የመርካቶ አራዳ)፣ ዳዊት ነጋ (ባባ ኤለን)፣ አስገኘው አሸኮ (ዲንዴሾ) እና በሀይሉ ባዩ (በሃይሉ ማታ) ታዳሚውን እንደሚያዝናኑ የገለፁት አቶ ታደሰ፤ ዲጄ ኪንግስተን (ወዝወዝ አዲስ)፣ ዲጄ ሼሪ፣ ዲጄ የሚ እና ዲጄ ሮፊም መድረኩን ያደምቁታል ብለዋል፡፡ ኮንሰርቱ የፌስቲቫል ይዘት እንደሚኖረው የተገለጸ ሲሆን ሁለት እውቅ ስጋ ቤቶች፣ ስምንት ሬስቶራንቶችና ስድስት ባሮች ይሳተፉበታልም ተብሏል፡፡ የመግቢያ ዋጋ እስከ አርብ 12 ሰዓት ለሚገዙ መደበኛው 200 ብር፣ ቪአይፒ 500 ብር ሲሆን በዕለቱ ትኬት ለሚገዙ መደበኛው 300 ብር እንደሚሆንና ቪአይፒው ላይ ጭማሪ እንደማይደረግ ተነግሯል፡፡ ቦሌ የሚገኘው ፋና ፓርክ 10ሺህ ሰዎችን የመያዝ አቅም እንዳለው የተገለፀ ሲሆን ይህም ህዝቡ ሳይጨናነቅ እንደ ልቡ እንዲዝናና ያደርገዋል ተብሏል፡፡ ቢጂአይ ኢትዮጵያ የኮንሰርቱ የክብር ስፖንሰር እንደሆነ ታውቋል፡፡

Read 1347 times