Saturday, 18 June 2016 13:12

የ8 አመቱ ኢትዮጵያዊ በ5ሺህ ሜትር የዓለም ክብረወሰን አስመዘገበ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

- እስካሁን 6 ክብረ ወሰኖችን አስመዝግቧል
- ከወራት በፊት የአመቱ ምርጥ አትሌት ተብሏል

በአሜሪካ የ3ኛ ክፍል ተማሪ የሆነውና የ8 አመት ዕድሜ ያለው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ታዳጊ ታም ጋቬናስ፤ ባለፈው ሳምንት በኒውዮርክ በተካሄደው የኬንዝ ዶላን መታሰቢያ የ5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር አዲስ የአለም ክብረወሰን ማስመዝገቡን ያሁ ኒውስ ዘግቧል፡፡
ታዳጊው የ5ሺህ ሜትር ሩጫውን በ18 ደቂቃ በማጠናቀቅ፣በዚህ ዕድሜ ርቀቱን ፈጥኖ የጨረሰ የዓለማችን ባለተስፋ ታዳጊ አትሌት ተብሏል ያለው ዘገባው፤ታዳጊው ከሶስት አመታት በፊትም በዚያው በአሜሪካ በተካሄደ የ5 አመት ዕድሜ ያላቸው ታዳጊዎች የሩጫ ውድድር ላይ በ800 ሜትርና በ1ሺህ 500 ሜትር አዲስ የዓለም ክብረወሰን ማስመዝገቡን አስታውሶ፣ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በርካታ ሽልማቶችን ማግኘቱንና መነጋገሪያ መሆኑን አስታውቋል፡፡  
ባለፈው አመት በ800 ሜትር፣ በ1ሺህ 500 ሜትርና በ400 ሜትር ውድድሮች አዳዲስ ብሄራዊ ክብረ ወሰኖችን ያስመዘገበው ታዳጊው፤ከወራት በፊትም በአሜሪካ በተካሄደው ዩኤስኤቲኤፍ አመታዊ የታዳጊ አትሌቶች ሽልማት፣የአመቱ ምርጥ አትሌት ተብሎ መሸለሙም ታውቋል፡፡  
ታም ጋቬናስ በኢትዮጵያ እንደተወለደና ዕድሜው ሶስት አመት ሳይሞላው፣ ሜሪ ሊዛ ጋቬናስ በተባለቺው አሜሪካዊት አማካይነት በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካ መወሰዱን ያስታወሰው ያሁ ኒውስ፣ አሳዳጊው የተፈጥሮ ክህሎቱን በማጤን ለስኬት እንዲታትር ታበረታታው እንደነበር ጠቁሟል፡፡

Read 6568 times