Saturday, 16 July 2016 13:22

‹‹ከኒያ ልጆች ጋር›› ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በደርግ ስርዓት የኢህአፓ ታጋይ ሆነው ለእስርና ለእንግልት ስለተዳረጉ ወጣቶች የሚተርከው ‹‹ከኒያ ልጆች ጋር›› የተሰኘ መፅሐፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡ ከአባላቱ አንዱ በነበረው ትንሳኤ የተባለ የኢህአፓ ታጋይ ጋር በተደረገ ቃለ ምልልስ፣ በፋሲካ መለሰ የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ባለታሪኩ በእስርና በስደት ባሳለፈው ህይወት ላይ ተመስርቶ ስለ ሌሎች ተመሳሳይ ህይወት ያሳለፉ ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች የሚተርክ ሲሆን ወጣቶቹ ምን አይነት ገድል እንደፈፀሙ፤እንዴት እንደታሰሩና እንዴት እንደተፈቱ በስፋት ይተነትናል ተብሏል፡፡ በ17 ምዕራፎች  የተከፋፈለው መፅሐፉ፤ በፋርኢስት ማተሚያ ቤት ታትሞ በክብሩ መፅሐፍ መደብር እየተከፋፈለ ሲሆን በ90 ብር ከ99 ሳንቲም ለአገር ውስጥና በ20 ዶላር በውጭ አገራት ለገበያ መቅረቡ ታውቋል፡፡

Read 1277 times