Saturday, 10 September 2016 15:25

ኒጀር አህያ ኤክስፖርት ማድረግን ከለከለች

Written by 
Rate this item
(2 votes)

- በአገሪቱ የአህዮች ዋጋ በ3 እጥፍ አድጓል
      በኒጀር አህዮችን ወደ ውጭ ገበያ የሚልኩ የንግድ ተቋማት መበራከታቸውንና የአገሪቱ አህዮች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መመናመኑን ተከትሎ የኒጀር መንግስት ባለስልጣናት የአህያ ኤክስፖርትን የሚከለክል ህግ ማውጣታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ የንግድ ተቋማት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አህዮችን ወደ ሌሎች አገራት በመላክ ከፍተኛ ትርፍ እያገኙ እንደሆነ የጠቆመው ዘገባው፤ የአገሪቱ አህዮች በብዛት የሚላኩት ወደ እስያ አገራት መሆኑንና ቀዳሚውን ስፍራ የምትይዘውም ቻይና እንደሆነች ገልጧል፡፡ ባለፈው አመት ለውጭ ገበያ የቀረቡ የኒጀር አህዮች ብዛት 27 ሺህ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻም ከ80 ሺህ በላይ የአገሪቱ አህዮች ወደተለያዩ የአለማችን አገራት መላካቸውን ጠቁሟል፡፡
አህያ በተለይ በአገሪቱ የገጠር አካባቢ ማህበረሰብ ዋነኛ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ የኒጀር መንግስት ባለስልጣናትም አህዮችን በብዛት ለውጭ ገበያ ማቅረቡ በዚሁ ከቀጠለ አስጊ ሁኔታ ይፈጠራል በሚል የውጭ ንግዱን የሚከለክል ህግ ማውጣታቸውን አመልክቷል፡፡ የውጭ ንግዱ መስፋፋቱን ተከትሎ ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ በአገሪቱ የአህዮች ዋጋ በሶስት እጥፍ ያደገ ሲሆን በኒጀር አንድ አህያ እስከ 150 ዶላር ዋጋ እንደሚያወጣ ዘገባው አስታውቋል፡፡

Read 1432 times