Sunday, 18 September 2016 00:00

ዛሬ ‹‹በጋላኒ ቡና›› የሙዚቃ ድግስ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   ከወራት በፊት የአሲድ ጥቃት ለደረሰባት ወጣት መሰረት ንጉሴ ህክምና የሚውል ገቢ ማሰባሰቢያ የሙዚቃ ድግስ ጀክሮስ አካባቢ በሚገኘው ጋላኒ ኮፊ ውስጥ ከቀኑ 8 ሰዓት እስከ 12 ሰዓት እንደሚካሄድ አዘጋጁ ሴታዊት ንቅናቄ ገለፀ፡፡ በመዚቃ ድግሱ ላይ ፀደንያ ገ/ማርቆስ፣ ማርታ ታደሰና ቼሊና የሚያቀነቅኑ ሲሆን በድግሱ ላይ ለመታደም መግቢያ በነፃ እንደሆነ ታውቋል፡፡ ከሙዚቃ ድግሱ በተጨማሪ የስዕልና የፎቶግራፍ ሽያጭ የሚካሄድ ሲሆን ገቢው ሙሉ በሙሉ ለተጎጂዋ እንደሚሆን ከሴታዊት ንቅናቄ መስራቾች አንዷ የሆኑት  ዶ/ር ስሂን ተፈራ ገልጸዋል፡፡ በዝግጅቱ ላይ በጥቃት መከላከል ላይ የሚሰሩ የድርጅት ተወካዮች፣ የመንግስት ሃላፊዎች፣የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን ተጎጂዋ በቦታው ተገኝታ ንግግር እንደምታደርግም ታውቋል፡፡ ማንኛውም ጉዳዩ ይመለከተኛል የሚል አካል በፕሮግራሙ ላይ ተገኝቶ፣ለተጠቂዋ ወገናዊነቱን እንዲያሳይ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Read 800 times