በቀድሞው አንድነት ፓርቲ ውስጥ ጉልህ ሚና በነበራቸው አቶ አበበ አካሉ የተፃፈው ‹‹የቤልሆር ሹመኞች›› የተሰኘ ፖለቲካዊ ልብወለድ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ በምድር ላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ እንዲሁም የሰማዩን ኑሮ የሚያስቃኝ ነው ተብሏል፡፡ በ256 ገጾች የተመጠነው መፅሀፉ ለአገር ውስጥ በ81 ብር፣ለውጭ አገራት በ20 ዶላር ገበያ ላይ ቀርቧል፡፡ የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አፈጉባኤ.፣በኋላም የሰማያዊ ፓርቲ የውጭ ግንኙነት ሀላፊ የነበሩት ደራሲው፤ቀደም ሲል “የሲኦል ፍርደኞች ቁ-1” የተሰኘ መጽሃፍ ለንባብ ማብቃታቸው የሚታወስ ሲሆን ‹‹ጉዞ ወደ ሲኦል ፍርደኞች ቁጥር 3›› ለማሳተም በዝግጅት ላይ መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና