Sunday, 16 October 2016 00:00

የቱርክ መንግስት 125 የፖሊስ መኮንኖችን አሰረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     ባለፈው ሃምሌ ወር ከተቃጣበትና ከከሸፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር በተያያዘ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ዜጎቹን ማሰሩን የቀጠለው የቱርክ መንግስት ባለፈው ማክሰኞም ተጨማሪ 125 የፖሊስ መኮንኖችን ማሰሩን ሮይተርስ ዘገበ፡፡
የፖሊስ መኮንኖቹ እንዲታሰሩ የተወሰነባቸው ባይሎክ የተሰኘውንና በመፈንቅለ መንግስቱ ጠንሳሽ የሆነው ቡድን ደጋፊዎች የሚጠቀሙበትን የአጭር የጽሁፍ መልዕክት ማስተላለፊያ የሞባይል አፕሊኬሽን ሲጠቀሙ ተገኝተዋል በሚል መሆኑን ዘገባው ገልጧል፡፡
የመንግስት ሃይሎች ማክሰኞ ዕለት በመዲናዋ ኢስታንቡል የፖሊስ መኮንኖችንን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን  የጠቆመው ዘገባው፣ ከታሰሩት መካከልም 30 ያህሉ ምክትል የፖሊስ አዛዦች እንደሆኑ ገልጧል፡፡
የአገሪቱን የፍትህ ሚኒስትር ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው ባለፉት ወራት ከከሸፈው መፈንቅለ መንግስት ጋር ንክኪ አላቸው በሚል የተጠረጠሩ 32 ሺህ ያህል የወታደራዊ ሃይል መኮንኖች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ዳኞች፣ መምህራንና ሌሎች ባለሙያዎች ታስረዋል፡፡

Read 1033 times