Sunday, 22 January 2017 00:00

‹‹ኢትዮጵያዊነት፤ አሰባሳቢ ማንነት በአንድ አገር ልጅነት›› ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ደራሲና ጋዜጠኛ ዩሱፍ ያሲን የፃፈውና በማንነት ጥያቄዎች ዙሪያ ያሉትን ውስብስብ ክርክሮች አሰባስቦ በመያዝ፣ መፍትሄዎችን ያመላክታል የተባለው ‹‹ኢትዮጵያዊነት፣ አሰባሳቢ ማንነት በአንድ አገር ልጅነት›› የተሰኘ መፅሃፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሀፉ በተለይም የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ከተጋረጠባት ውስብስብ የማንነት ጥያቄ አንፃር የሚያስጨንቁና መፍትሄ የሚሹ ጉዳዮች በጥልቀት የተተነተኑበት ነው ተብሏል፡፡ የመጽሀፉ የመጀመሪያ ዕትም በውጭ አገር ለገበያ የቀረበ አንደነበር የተገለፀ ሲሆን የያዘው ቁም ነገር በውጭ አገር ተገድቦ እንዳይቀርና ኢትዮጵያዊያን በስፋት እንዲያወያዩበት ታስቦ፣ ሁለተኛው እትም አገር ቤት መሰራጨቱም ታውቋል፡፡ በበርካታ ምዕራፎችና ንዑስ ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ437 ገፆች የተቀነበበው፤ መፅሁፉ በ131 ብር ከ60 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 2351 times