Sunday, 22 January 2017 00:00

“ፍናን” አዲስ አልበም ሐሙስ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  የአልበሙ ሽያጭ ሙሉ ለሙሉ ለፌስቱላ ህሙማን ይውላል
    በሰርከስ ትግራይ ውስጥ ያደገው የወጣቱ ኢሳቅ ኪ/ማሪያም “ፍናን” የትግርኛ አልበም የፊታችን ሐሙስ ድምፃዊው ላለፉት ሰባት አመታት እየሰራበት ባለው ‹‹ክለብ ፍሪደም›› ይመረቃል፡፡ በቅርቡ ለገበያ የቀረበው አልበሙ 400 ሺህ ብር እንደወጣበት የገለፀው ድምፃዊ ኢሳቅ፤ የአልበሙ ሽያጭ ሙሉ ለሙሉ ለፌስቱላ ህሙማን እንደሚውል ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ 12 የትግርኛ ዘፈኖችን ያካተተው ‹‹ፍናን›› 16 የሙዚቃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ በርካታ አመታት ፈጅቷል ተብሏል፡፡ በቀጣይ በመቀሌና በአውሮፓ እንደሚመረቅ አስተባባሪው አቶ ተስፋዬ ገ/ዮሀንስ ገልጸዋል፡፡ የአልበሙ ስያሜ “ፍናን” የግዕዝ ቃል ሲሆን ሞራል (ወኔ) የሚል ፍቺ እንዳለው ተጠቁሟል፡፡

Read 1753 times