Saturday, 26 August 2017 12:18

የ“ሆሄ” አሸናፊዎች ሰኞ ይሸለማሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ኖርዝ ኢስት ኤቨንትስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከብሄራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ- መፃህፍት ኤጀንሲ ጋር በተመባበር፣ ሲያካሂድ የቆየው የሥነፅሁፍ ውድድር፣ ሰኞ ከምሽቱ 12፡ 00 እስከ 2፡00 በሚዘልቅ የሽልማት ሥነ ስርዓት እንደሚጠናቀቅ ተገለፀ፡፡ የሽልማት ድርጅቱ፤ በረጅም ልብ ወለድ፣ በግጥም፣ በልጆች
መፃህፍት እንዲሁም ለስነፅሁፍ እድገት፤ ለንባብና ትምህርት መስፋፋት የላቀ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት የሚሉትን ጨምሮ በዘጠኝ ዘርፎች ሥራዎችን ሲያወዳድር የቆየ ሲሆን ከነገ በስቲያ የየዘርፉ አሸናፊዎች ይፋ እንደሚሆኑና እንደሚሸለሙ ታውቋል፡፡ የሽልማት ሥነስርዓቱ በኪነ-ጥበባዊ ዝግጅቶች ታጅቦ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ በዕለቱ የስነ ፅሁፍ ባለሙያዎች፣ የተሸላሚ ቤተሰቦች፣ የስነ-ፅሁፍ አቅራቢዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙ ሲሆን የብሄራዊ ቴአትር በር ከቀኑ 11፡00 እስከ 12፡00 ብቻ ክፍት እንደሚሆን የገለፁት አዘጋጆች፤ ታዳሚዎች በሰዓቱ እንዲገኙ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

Read 2400 times