Sunday, 13 May 2018 00:00

የመጀመሪያው አገር አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን ሽልማት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ የመገናኛ ብዙኃን ሽልማት ሊካሄድ መሆኑን የሽልማት አዘጋጁ ዋይጂኤስ መልቲ ሚዲያ አስታወቀ፡፡ የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ በብሮድካስት ባለስልጣን እውቅና እንዳገኘ የገለፁት የድርጅቱ ኃላፊዎች፤  የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ነሐሴ 26 ቀን 2010 ዓ.ም በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ እንደሚካሄድ ጠቁመዋል፡፡
በዕለቱም በህትመት፣ በብሮድካስትና በድረ ገፅ መገናኛ ብዙኃን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉና የተመረጡ ጋዜጠኞች እንደሚሸለሙ ተገልጿል፡፡ ተሸላሚዎች የሚመረጡት በዘርፉ የካበተ ልምድና ብቃት ባላቸው የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ዳኝነት እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡ የሽልማቱ አዘጋጅ ዋይጂኤስ መልቲ ሚዲያ ከአሁን በፊት የተለያዩ የኪነ ጥበብ መድረኮችን በማዘጋጀት የሚታወቅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በብስራት ኤፍ ኤም ሬዲዮ ላይ “ማራኪ” የተሰኘ ፕሮግራም የሚያቀርብ ድርጅትም ነው፡፡

Read 3560 times