Saturday, 26 May 2012 12:34

ጄይ ዚና ካናዬ ዌስት በራፕ ንግስና ተሟገቱ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(4 votes)

ይዚና ካናዬ ዌስት ባለፈው ሰኞ ለንደን ውስጥ በሚገኘው የኦ2 ስታድዬም ባቀረቡት ኮንሰርት በሙዚቃቸው ለራፕ ንግስና እንደተሟገቱ ዘ ሚረር ዘገበ፡፡ ሁለቱ ራፕሮች አምና ባወጡት የጋራ አልበማቸው “ዎች ዘ ትሮን” የተሰየመ የኮንሰርት ዝግጅታቸው በመላው አውሮፓ በመዘዋወር ለ5 ሳምንታት ያቀርባሉ፡፡ የመጀመርያ ዝግጅታቸውን ባለፈው ሰኞ እና ማክሰኞ በለንደን ጀምረዋል፡፡ በዝግጅታቸው ከ110 በላይ ዘፈኖች ያቀረቡ ሲሆን በተለይ “ኒጋርስ ኦን ፓሪስ” የተባለው ዘፈን ለ32 ደቂቃ ተጫውቶታል፡፡  ራፕሮቹ ባለፈው ሃሙስ በስውዘርላንድ፤ ዛሬ በዴን ማርክ እንዲሁም ከሰኞ በኋላ በኖርዌይ ስዊድን፤ ፈረንሳይ_ ጀርመንና ቤልጅዬም በመዘዋወር እንደሚሰሩ ይጠበቃል፡፡ ዘ ሚረር እንደዘገበው ሁለቱ ራፕሮች   በኦ2 ስታድዬም 20 ጫማ ከፍታ ባላቸው ሁለት መድረኮች መድረክ ከ20ሺ በላይ ለነበረ ታዳሚያቸው ስራዎቻቸውን ሲያቀርቡ ንግስናው የማነው በሚል በራፕ ስንኞቻቸው ተሟግተዋል፡፡

ዘጋርደያን ከሁለቱ ራፕሮች ማን ይበልጣል በሚል ከአንባቢዎቹ ድምፅ አሰባስቦ በሰራው ዘገባ ጄይዚ በ54 በመቶ ድምጽ 46 በመቶ ያስመዘገበውን ካናዬ ዌስት መብለጡን ሲያትት ካናዬ ዌስት ከራፕርነት ይልቅ ምርጥ የፊልም ፕሮዲውሰር መሆኑን ገልፆ የራፕሮች ንጉስ ያለጥርጥር ጄይ ዚ ነው በሚል ደምድሟል፡፡ከዓመት በፊት ለገበያ የበቃው የጄይ ዚ እና የካናዬ የጋራ አልበም ‹ዎች ዘ ትሮን› በሰሜን አሜሪካ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ቅጂ የተሸጠ ሲሆን በመላው ዓለም በነበረው ገበያ ከ50 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደተገኘበት ይገለፃል፡፡

እሰከ 2015 እኤአ ያለው ሃብት 1 ቢሊዮን በመድረስ የመጀመርያው ጥቁር አሜሪካዊ ራፕር ሊሆን እንደሚበቃ የተተነበየለት ጄይዚ አምና ፎርብስ ባወጣው የራፕሮች ሃብት ደረጃ  ባስገባው 37 ሚሊዮን ዶላር መሪ ነው፡፡ ካናዬ ዌስት በበኩሉ 35 ሚሊዮን ዶላር ካስመዘገበው ፒ ዲዲ ቀጥሎ በ16 ሚሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢው ሶስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሙዚቃ ሙያው 23 ዓመታትን ያስቆጠረው የ42 ዓመቱ ጄይዚ 11 አልበሞችን የሰራና በመላው አለም 50 ሚሊዮን ቅጂ የሸጠ ራፕር ሲሆን 14 የግራሚ ሽልማቶችን የሰበሰበ ነው፡፡ የ34 ዓመቱ ካናዬ ዌስት በበኩሉ በሙያው 16 ዓመታትን ሲያሳልፍ 6 አልበሞች ከመስራቱ ም በላይ በዲጅታል ገበያ በአሜሪካ ብቻ 30 ሚሊዮን ዘፈኖችን የሸጠና 18 የግራሚ ሽልማቶችን በመሰብሰብ በሽልማቱ ታሪክ ከፍተኛውን ክብር ያገኘ ነው፡፡

 

 

Read 2456 times Last modified on Saturday, 26 May 2012 12:37