Saturday, 19 October 2019 12:29

በቅርብ በሚገኝ ሰው በ ሴቶች ላይ የሚደርስ ጥቃት ለጤና ያሳስባል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 ሴቶች ቅርብ በሆነ ጉዋደኛ ወይንም የትዳር አጋር የሚደርስባቸው ጥቃት ከጤናቸው መጉዋ ደል ጋር እንደሚገናኝ የአለም የጤና ድርጅት እ.ኤ.አ 29 November 2017 ባወጣው መረጃ ጠቅሶአል፡፡ መረጃው እንደሚያመለክተውም፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ሴቶች በመሆናቸው ብቻ የሚደርስባቸው ሲሆን ውጤቱም በአካል፤በሞራል፤እና በወሲብ የሚደርስ ጉዳት ተብሎ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እንደዚህ ያሉ ማስፈራራትን የጨመሩ ድርጊቶች ወይንም ኃይልን፤በማንኛውም ጊዜ በድንገት በግልም ይሁን ህብረተሰቡ ባለበት የሚፈጸሙ ነጻነትን የሚጋፉ ድርጊቶች ናቸው፡፡
በቅርብ ያለ ኑሮን የሚጋራ ጉዋደኛ ወይንም ባል የሚያደርሰው ጉዳት አካላዊ ጥቃት እና በጉልበት ወይንም በኃይል ወሲብ መፈጸም፤እንዲሁም በስነልቡና ላይ ከፍተኛ ጉዳት የመሳሰሉት ናቸው፡፡
ወሲባዊ ጥቃት በማንኛውም መንገድ ከግለሰብ ፈቃደኝነት ውጭ በጉልበት ወይንም በኃይል አስገድዶ መፈጸምን የሚመለከት ሲሆን ይህ በቅርብ ሰው ወይንም ኑሮን በሚጋራ ብቻ ሳይሆን በማንኛውም ሰው ሲፈጸም የሚገለጽበት ነው፡፡ ይላል የአለም የጤና ድርጅት የተባበሩት መንግ ስታትን መረጃ በመጥቀስ፡፡
ሴቶች በቅርባቸው ባለ ወንድ ሲጎዱ ማየት በአለም ላይ ምን ያህል የተተስፋፋ ችግር መሆኑን የሚያሳየው መረጃ በለንደን የሚገኘው(London School of Hygiene and Tropical Medi- cine እና በደቡብ አፍሪካ  (the South Africa Medical Research Council) ጠቅሶ በ80 ሀገራት ላይ መረጃ በመሰብሰብ ውጤቱም በአለም አቀፍ ደረጃ ከሶስት ሴቶች አንድዋ ማለትም ከአለም ሴቶች ወደ 35 % የሚሆኑት በሕይወት ዘመናቸው በቅርብ በሚገኝ ወይንም በማንኛ ውም ሰው ወሲባዊ ጥቃት እንደደረሰባቸው ይጠቁማል (እ.ኤ.አ 2013 WHO)፡፡
ከላይ እንደተጠቀሰው በአለም ላይ ካሉት ሴቶች አንድዋ በሕይወት ዘመንዋ በቅርብዋ በሚገኝ ወይንም በማንኛውም ሰው አካላዊ ወይንም ወሲባዊ ጥቃት ደርሶባታል ሲባል ወደ 23.2% የሚሆነው ከፍተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት የደረሰ ሲሆን ወደ 24.6% የሚሆነው ደግሞ በምእ ራብ የፓሲፊክ አገራት እንዲሁም 37% በምስራቅ ሜዲትሬንያን አካባቢ እና 37.7 % የሚሆነው ደግሞ በደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት እንደሆነ የአለም የጤና ድርጅት ይገምታል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ ወደ 38%የሚሆኑት ግድያዎች ሴቶች በቅርባቸው ባለ ሰው የደረሰባቸው መሆኑ እና ምንም እንኩዋን ቅርበት ከሌላቸው ሰዎች የደረሱ ጉዳቶችን በግልጽ የሚያሳይ መረጃ ባይኖርም ወደ 7% የሚሆኑ ሴቶች ተገደው የተደፈሩ መሆናቸውን ሪፖርት ያሳያል፡፡ ይሁን እንጂ ሴቶች በቅርባቸው ባሉ ወንዶች የሚደርስባቸው ወሲባዊ ጥቃት ለጉዳታቸው ከፍ ያለ ድርሻን እንደሚይዝ መረጃው ይጠቁማል፡፡
ለጉዳቱ ቁልፍ መረጃዎች ያላቸውን WHO እንደሚከተለው ዘርዝሮታል፡፡
በሴቶች ላይ የሚደርስ ጉዳት በተለይም በቅርብ አብሮ በሚኖር ወይንም በሚያገኛቸው ሰው የሚፈጸመው ከፍተኛውን የጤና ችግር የሚያስከትልና የሰብአዊ መብታቸውንም የሚጥስ ነው፡፡
በአለም እንደሚገመተው ከሶስት ሴቶች አንድዋ (30%) በሕይወት ዘመንዋ አካላዊ ወይንም ወሲባዊ ጉዳት ከቅርብ ወይንም አብሮአት ከሚኖር ሰው እንደሚደርስባት ተመዝግቦአል፡
በአለም አቀፍ ደረጃ በሴቶች ላይ ከሚደርሱ ግድያዎች 38% የሚሆኑት የሚፈጸሙት በወንድ የቅርብ ጉዋደኛ ወይንም የትዳር አጋር ነው፡፡
ጥቃት ሴቶችን አካላቸውን፤ ስነልቡናቸውን፤ ወሲባዊ ድርጊትን እና የስነተዋልዶ ጤናቸ ውን ሊጎዳ እንዲሁም በተለያዩ መንገዶች ለኤችአይቪ ሊያጋልጣቸው ይችላል፡፡
ወንዶች በሴቶች ላይ ጉዳት የሚያደርሱት በትምህርታቸው ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወይንም በልጅነታቸው ጥቃት እየደረሰባቸው ካደጉ፤በቤት ውስጥ ጥቃት ሲፈጸም እያዩ ካደጉ፤ ጎጂ በሆነ መንገድ አልኮሆል የሚወስዱ ከሆነ፤ የተዛባ የስነጾታ ልምድ ካላቸውና ዝንባሌያቸው ጥቃት ማድረስን የሚገፋፋ ከሆነ እና የሴቶች የበላይ ነኝ ብለው የሚያስቡ ከሆነ ድርጊቱን ይፈጽሙታል፡፡
ሴቶችም ጉዳት የሚደርስባቸው በትምህርታቸው ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ከሆነ  እና እናቶቻቸው ቅርብ በሆነው ወንድ ሲደበደቡ ወይንም ሲጎዱ እያዩ ካደጉ እንዲሁም በሕጻንነ ታቸው ጉዳት እየደረሰባቸው ካደጉ እና በወንድ መጠቃት ወይንም መደብደብ ትክክል ነው ብለው የሚቀበሉ ከሆነ፤ ለወንዶች የተለየ ክብር ከመስጠት፤እና ሴቶች በወንዶች ላይ ጥገኛ ከሆኑ ጉዳት ሲፈጸምባቸው እንደትክክለኛ ነገር ይወስዱታል፡፡
ስለዚህም ሴቶች ድጋፍ ከተደረገላቸው እና አቅማቸውን ለማጠናከር እርምጃ ከተወሰደ እና የምክር አገልግሎት ከተሰጣቸው እንዲሁም ጉዳት እንዳይደርስባቸው ለማድረግ ኑሮአቸውን የሚጎበኝላቸው ወይንም ቃል የሚገባላቸው ካገኙ ግንዛቤያቸው ስለሚያድግ ጥቃቱን ለማስቆም እንደሚተባበሩ እሙን ነው፡፡
አንዳንድ ሊፈጠሩ የሚችሉ ግጭቶች ወይንም ቀደም ሲል በደረሰ ጥቃት ምክንያት የተከሰተ መፈናቀል የመሳሰሉት ነገሮች በድጋሚ ለጉዳቱ እንዲዳረጉ የሚያስገድድበት ምክንያት ይኖራል:: እንደዚህ ያሉት ክስተቶች በቅርብ ሰዎች ወይንም በቅርብ በማይገኙ ሰዎችም ቢሆን በአዲስ መልክ በሴቶች ላይ ሊፈጠሩ የሚችሉ ጉዳቶች ናቸው፡፡
የሴቶችን በቅርብ ሰው መጠቃት ሁኔታ በአፍሪካ በተለይም ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት በተመሳሳይ የሚጠቀስ መሆኑን የ Arch Public Health. ይጠቁመናል:: በእርግጥ በጥቃቱ ምክን ያት የሚጎዱት ሴቶች ቁጥር ከፍ ያለ ነው፡፡ የሚደርስባቸውም የጤና እክል በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ ለምሳሌም በእርግዝና ወቅት የሚደርስ ጉዳት እንዲሁም በግብረስጋ ግንኙነት ምክ ንያት በሚተላለፉ በሽታዎች ሳቢያ የወሲብ ፍላጎትን ማጣት ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በሴቶች ላይ በቅርብ ሰው የሚደርሱ ጥቃቶች በየትኛውም ቦታ ባሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ተመሳሳይ ቢሆ ንም ደረጃውና መጠኑ ግን ሁኔታውን አሜን ብለው በሚቀበሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ እንደሚጨምር እና ከቦታ ቦታ ከሀገር ሀገር በመላው አለም እንደሚለያይ እሙን ነው፡፡
ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የሴቶች መጠቃት በከፍተኛ ሁኔታ የተመዘገበ ሲሆን በአለም ከተመዘገበው 30% ጉዳት 36% ድርሻ ይይዛል፡፡ በአፍሪካ ብዙ ሴቶች በሕይወት ዘመናቸው አብሮአቸው በሚኖር ወይንም ቅርብ በሆነ ሰው የሚደርስባቸው ጉዳት 45.6% ሲሆን የሚደርስባቸው ወሲባዊ ጥቃት ደግሞ በየትኛውም የአለም ክፍል ከሚኖሩ ሴቶች 11.9% ይሆናሉ፡፡ በሴቶች ላይ ቅርብ ባለ ሰው የሚደርስ ጥቃት በጤና ላይ አስቸጋሪ ሲሆን ይህም የሚገለጽበት ደረጃ በተለይም ልጅን በመውለድ በኩል ከስነልቡና ጤና ችግር እስከ ስነተዋልዶ ጤና መታወክ ሲያጋጥማቸው ይታያል፡፡
ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ያሉ ሴቶች በቅርባቸው ባለ ሰው በሚደርስ ጉዳት ወይንም ጥቃት ምክንያት ምንም እንኩዋን በውጤቱ ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ የአካል ጉዳት ደር ሶባቸው ቢታይ ሴቶቹ ለወንዶቹ የሚሰጡት ምላሽ የስነልቦና መዛባት ወይንም አስከፊ የሆነ እንጂ ወንዶቹም ተጎድተዋል የሚል አስተሳሰብ አይታይባቸውም፡፡ ይህም በችግሩ ምን ያህል እንደተጎዱ ወይንም እንደተበሳጩ የሚመሰክር ነው፡፡ መረጃው እንደሚጠቁመው በቅርብ ባሉ ሰዎች በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች እና በእርግዝና ወቅት የሚታዩ ችግሮች በጥብቅ ግንኙነት አላቸው፡፡
በቅርባቸው ባሉ ሰዎች በአካል ወይንም በወሲብ ጉዳት እንደደረሰባቸው መረጃ ያቀረቡ ሴቶች በብዛት ላልታቀደ ወይንም ላልተፈለገ እርግዝና ይጋለጣሉ፡፡
በሕይወት ዘመናቸው በቅርብ ባለ ሰው ጉዳት የደረሰባቸው ሴቶች ሕይወት የሌለው ልጅ መውለድ ወይንም እርግዝናው ካለቀኑ እና ሕይወት አልባ ሆኖ የመወገድ ወይንም ጽንስ መቋረጥ፤ የመሳሰሉት ችግሮች ይደርስባቸዋል፡፡
የተጎዱት ሴቶች የስነተዋልዶ ጤና ችግር በተለያዩ መንገዶች ሊገጥሙአቸው ይችላል፡፡ በግብ ረስጋ ግንኙነት ወቅት በሚተላለፉ በሽታዎች ከመያዝ እስከ እርግዝናን በጸጋ አለመቀበል በሚያደርስ ስጋት ውስጥ ሊጥላቸው ይችላል፡፡
በቅርብ ሰው በሴት ላይ የሚደርስ ጥቃት ኤች አይቪን ጨምሮ ለተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች ሊዳርግ ይችላል::
ከሌሎች የአለም ክፍሎች በተለየ በአፍሪካ ውስጥ በቅርብ ሰው በሴት ላይ የሚደርስ ጥቃት ከሚያስከትላቸው ችግሮች መካከል ከፍተኛ ለሆነ የመጠጥ ሱስ የመጋለጥ ፤ወይንም በልጅነት ጊዜ የሚደርስ ጥቃት፤ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ማለትም ስራ አጥነት እና መጨረሻ የሌለው በወንድ ቁጥጥር ስር የመሆን ልማድ ይታያል፡፡    

Read 9186 times