Saturday, 16 May 2020 11:23

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ ካሳ እንዲከፍለው ጠይቋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፈው አመት መጋቢት ወር ላይ ከተከሰተው የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ጋር በተያያዘ ለደረሰበት ኪሳራ እና አደጋው በመልካም ስምና ዝናው ላይ ላደረሰበት ጉዳት ካሳ እንዲከፈለው ለአውሮፕላኑ አምራች ኩባንያ ጥያቄ ማቅረቡን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የአየር መንገዱ የቦይንግ ምርቶች የሆኑት 737 ማክስ አውሮፕላኖች አደጋው መከሰቱን ተከትሎ፣ ከቴክኒክ ብልሽት ጋር በተያያዘ ከበረራ በመታገዳቸውና ስራ ፈትተው በመቆማቸው እንዲሁም፣ የግዢ ስምምነት የፈጸመባቸውን ሌሎች አውሮፕላኖች በወቅቱ ሊያስረክበው ባለመቻሉ ሳቢያ ለደረሰበት ኪሳራና ማግኘት ሲገባው ላጣው ገቢ ካሳ እንዲከፍለው ለቦይንግ ኩባንያ ጥያቄ ማቅረቡንና ክፍያው እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ይፈጸምልኛል ብሎ እንደሚጠብቅ የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
አየር መንገዱ ለቦይንግ ኩባንያ ምን ያህል ገንዘብ በካሳ መልክ እንዲከፈለው እንደጠየቀ ዘገባው ያለው ነገር የለም፡፡


Read 1186 times