ያንቺን ድምፅ ብቻ፣ ሲያቃጭል የኖረ
የቆለፍሺው ጆሮ፣ በምን ተሰበረ?
ይኸው ብዙ ድምፆች
ከየትም እየመጡ፣ ይሰሙኝ ጀመረ።
የዘጋሽው ልቤ!
የቆለፍሽው ልቤ!
የተሰባበረው
እንዴት ሰው አማረው?
። ። ።
ልረሣሽ ነው መሠል፣ ወይ ደግሞ
ልትመጪ
ይሰማኝ ጀመረ
ያውደኝ ጀመረ
ይታየኝ ጀመረ፣ ሕይወት ካንቺ ውጪ።
(በላይ በቀለ ወያ)
__________________
የዕድሜ ልክ ደብዳቤ
ይድረስ ለምወድሽ…
ዓለም ያክል ሐሳብ የተሸከመ ሰው፣
ዕረፍት አያገኝም ፍቅር ቢዳብሰው።
ቢሆንም እውነታው፣
ሞቴ አንች ነሽና…!
Published in
የግጥም ጥግ