የድረገጽ መረጃ መንታፊዎች ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የ106 አገራት ዜግነት ያላቸው የ533 ሚሊዮን የፌስቡክ ተጠቃሚ ደንበኞችን የግል ሚስጥራዊ መረጃዎች በመዝረፍ በይፋ ማሰራጨታቸውንና ይህም ተጠቃሚዎችን ለባሰ ጥቃት ይዳርጋል ተብሎ መሰጋቱን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
በድረገጾች በኩል ባለፈው ቅዳሜ በነጻ የተሰራጩት የፌስቡክ ተጠቃሚዎች ግላዊ መረጃዎች የተጠቃሚዎቹን ስሞች፣ የስልክ ቁጥሮች፣ የኢሜይል አድራሻዎችና ሌሎች ሚስጥራዊ መረጃዎችን ያካተቱ እንደሆኑ የጠቆመው ዘገባው፣ የስልክ እንዲሁም የኢ-ሜይል አድራሻዎችን ጨምሮ ሌሎች ግለሰባዊ ሚስጥሮችንም ያካተቱ ናቸው ተብሏል፡፡
መረጃዎቻቸው በድረገጽ መንታፊዎች ተዘርፈው ይፋ ከተደረጉባቸው የፌስቡክ ደንበኞች መካከል 32 ሚሊዮን ያህሉ በአሜሪካ፣ 11 ሚሊዮን የሚሆኑት በብሪታኒያ፣ 6 ሚሊዮን ያህሉ ደግሞ በህንድ እንደሚገኙ የጠቆመው ዘገባው፤ ፌስቡክ በበኩሉ መረጃው ተዘርፎ ወጣ መባሉን እንዳስተባበለ አመልክቷል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና