Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 01 September 2012 11:58

የሌሊሳ ግርማ “አፍሮጋዳ” ለገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአዲስ አድማስ ጋዜጣ በሚጽፋቸው አጫጭር ልብወለዶች ወጐች የሚታወቀው ሌሊሳ ግርማ “አፍሮጋዳ” በሚል ርዕስ አዲስ መፅሃፍ አሳትሞ ሰሞኑን ለገበያ አቀረበ፡፡ መጽሐፉ በአራት ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን የሀበሻ ባህል፣ ጥበብ፣ ሀሳብ ላይ ያተኮሩ ማሰላሰሎችና የፖለቲካ ወጐች የሚል ርዕስ ተሰጥቷቸዋል፡፡

“በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የተካተቱት መጣጥፍ (ወግ) ሀሳቦች…በስድስት አመት ጊዜ ውስጥ የተፃፉ የግል እይታዎቼ ናቸው፡፡ ነገር ግን የግል ዕይታም ቢሆን የሚመነጨው ከአጠቃላይ የተጨባጭ እውነታ ነው፡፡ በአጭሩ ከእናንተ፡፡ ባይሆን ኖሮ እኔም የምጽፍበት እናንተም የምታነቡበት ምክንያት ባልኖረ ነበር” ብሏል ሌሊሳ ግርማ - በመፅሃፉ፡፡ በመጽሐፉ ጀርባ ላይ አስተያየት የሰጠው አንጋፋው ደራሲ አዳም ረታ፤ “የሌሊሳን ሱሪያሊስት ምናባዊ ግራ ገብ ታሪኮች የተወሰኑትን ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ አንብቤአለሁ፡፡ ራሳቸውን የቻሉ ወጥ እና አጫዋች በመሆናቸው እወዳቸዋለሁ…የሱን ጽሑፍ ከተለመዱት የሥነጽሑፍ ዘዬዎች አንፃር መመልከት ይከብዳል፤ የአፃፃፍ ስልቱ ከየትኛው ዓይነት የሥነ ጽሑፍ ዝርያ የበቀለ እንደሆነ መግለጽ ማለቴ ነው፡፡” በማለት ስለ ፅሁፎቹ ያብራራል፡፡ ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን በበኩሉ በሰጠው አስተያየት፤ “ሌሊሳ ግርማ በአፃፃፍ ስልቱ ከተለመደው ወጣ ይላል፡፡ ሆኖም ወጣ ላሉት ብቻ ሳይሆን ገባ ላሉትም ይጥማል” ብሏል፡፡ በ197 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ በ39 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

ደራሲው ከዚህ ቀደም “የነፋስ ህልም” የተሰኘ የአጫጭር ልብወለዶች መድበል ለንባብ ማቅረቡ ይታወቃል፡፡

 

 

Read 1300 times Last modified on Saturday, 01 September 2012 12:00