Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 08 September 2012 12:57

ኦፕራ በከፍተኛ ክፍያ ትመራለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኦፕራ ዊንፍሬይ ከፍተኛ ክፍያ በማግኘት የመዝናኛውን ኢንዱስትሪ በቀዳሚነት እንደምትመራ ፎርብስ መፅሄት አመለከተ፡፡ ካለፈው አመት ጀምሮ አዲስ በከፈተችው ‹ኦውን› የተባለ የቴሌቭዥን ኔትዎርክ ስኬታማ ለመሆን ያልቻለችው ኦፕራ፤ ዘንድሮ 165 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት መሪነቱን መያዟን የገለፀው ፎርብስ፤ ከፍተኛውን ክፍያ በማግኘት የመዝናኛ ኢንዱስትሪውን ስትመራ ለአራተኛ ተከታታይ ዓመት መሆኑን ገልጿል፡፡ የኦፕራ ዊንፍሬይ ገቢ ከዓምናው በ125 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ ማሳየቱንም ፎርብስ ጨምሮ ዘግቧል፡፡ በክፍያ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ‹‹ትራንስፎርመርስ፡ ዳርክ ኦፍ ዘሙን› የተባለውን ፊልም ዲያሬክት ያደረገው ማይክል ቤይ ሲሆን 160 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንዳገኘ ታውቋል፡፡

ሌላው ታዋቂ የፊልም ዲያሬክተር ስቲቨን ስፒልበርግ ዘንድሮ ለእይታ በበቁለት ‹ዘ አድቬንቸርስ ኦፍ ቲን ቲን› እና ‹ዋር ሆርስ› በተባሉ ፊልሞቹ እንዲሁም ‹ዘ ስማሽ› በተባለ የቴሌቭዥ ቶክ ሾው ባገኘው 130 ሚሊዮን ዶላር 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ የፓይሬትስ ኦፍ ካረቢያን ፊልሞች ዲያሬክተር ጄሪ ብሩክ ሄበር በ115 ሚሊዮን ዶላር ገቢው 4ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ፤ ራፕሩ ዶር ድሬ ‹ቢትስ› በተባለ የጆሮ ማዳመጫ አምራች ኩባንያው አማካኝነት ባገኘው 110 ሚሊዮን ዶላር ገቢ  አምስተኛ ደረጃ መውሰዱን የፎርብስ ሪፖርት አመልክቷል፡፡ በአሜሪካ የቴሌቭዥን ንግስት በሚል የምትታወቅው ኦፕራ ባላት የሃብት መጠን  ቀዳሚዋ ጥቁር አሜሪካዊ ስትሆን እስከ 2.7 ቢሊዮን ዶላር እንዳካበተች ይነገርላታል፡፡

 

Read 2611 times