Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 08 September 2012 13:01

“ዣንቶዣራ”፣ “ታዳኤል”፣ “ሽሙጦች 3” ለንባብ ቀረቡ

Written by 
Rate this item
(21 votes)

በአንባቢያን ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን የተቀዳጀው “ዴርቶጋዳ” መፅሐፍ ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ የልብወለዱን ሦስተኛ ክፍል ለንባብ አበቃ፡፡ “ዣንቶዣራ” በሚል ርእስ የቀረበው 304 ገፆች ያሉት ልብወለድ መፅሐፍ ለአገር ውስጥ ገበያ በ45 ብር፣ ለውጭ ገበያ ደግሞ በ25 ዶላር ቀርቧል፡፡ ይስማዕከ ከ”ዴርቶጋዳ” በተጨማሪ “ራማቶሃራ”፣ “ተልሚድ”፣ “የቀንድ አውጣ ኑሮ”፣ “የወንድ ምጥ” እና “ተከርቸም” የተሠኙ መጻሕፍት አሉት፡፡  በደራሲ አዳም ረታ ከሦስት ዓመት በፊት ለንባብ በቅቶ የነበረው “እቴሜቴ የሎሚ ሽታ” የአጫጭር ልቦለዶች መድበል በድጋሚ ታትሞ ለንባብ በቃ፡፡ ምናባዊ ማጣቀሻ መፃሕፍትን በመጠቀም እና በአፃፃፍ ስልቱ ከመደበኛው አፃፃፉ ወጣ ያለው የአዳም መፅሐፍ፤ ሰባት አጫጭር ልቦለዶች አሉት፡፡ 318 ገፆች ያለው መጽሐፍ 45 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ በቅርቡ “የሎሚ ሽታ” የሚለው መፅሃፍ ላይ የተመሰረተ የአማርኛ ፊልም መሠራቱ ይታወቃል፡፡

ታዋቂው ደራሲ አዳም ረታ ካሁን ቀደም ለብቻው ያሳተማቸው “ማህሌት”፣ “ግራጫ ቃጭሎች”፣ “አለንጋና ምስር”፣ “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር” እና “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” የሚሉ መፃሕፍትና ከሌሎች ፀሐፍት ጋር ያዘጋጀው በርካታ መፃሕፍት አሉት፡፡  “የአቤ ቶክቻው ምፀቶች ሽሙጦች 3” በሚል ርእስ በአበበ ቶላ የተዘጋጀው ፖለቲካዊ መፅሐፍ 36 ታሪኮችን የያዘ ሲሆን 175 ገፆች አሉት፡፡ የመፅሐፉ ዋጋ 35 ብር ነው፡፡ በስደት ከሚገኝበት ሃገር መፅሐፉን ያዘጋጀው አበበ ቶላ፤ አንዳንዶቹን ታሪኮች በማህበራዊ ድረገፅ ሲያስነብብ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በተያያዘ ዜና በእርቅይሁን በላይነህ የቀረበው “ታዳኤል” የተሰኘ ረዥም ልቦለድ ከትናንት ጀምሮ ለንባብ በቃ፡፡ 256 ገፆች ያሉት መፅሐፍ ብሔራዊ ስሜት ላይ እንደሚያተኩር ደራሲው ገልጿል፡፡ የመፅሐፉ ዋጋ 44 ብር ነው፡፡ በሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ድራማዎች ፀሐፊነቱ የሚታወቀው እርቅይሁን፤ ካሁን በፊት “ያልተጠቡ ጡቶች” የተሰኘ የአጭር ልቦለድ መፅሐፍ አሳትሟል፡፡

 

 

Read 10598 times Last modified on Saturday, 08 September 2012 13:03