Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 29 September 2012 09:56

“ክራር ኮሌክቲቭ” አዲስ አልበም አወጣ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ተቀማጭነቱን በለንደን ያደረገው ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ባንድ “ክራር ኮሌክቲቭ” የመጀመሪያ አልበም ለገበያ በቃ፡፡ “ኢትዮጵያ ሱፐር ክራር” የሚል መጠሪያ የተሰጠው አልበሙ ለዓለም ገበያ የቀረበው ከ15 ቀናት በፊት ሲመሰረት በአሳታሚው ዎርልድ ሚውዚክ ኔትዎርክ አማካኝነት ነው፡፡ ክራር ኮሌክቲቭ በሦስት የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች የተመሰረተ ሲሆን እነሱም የሙላቱ አስታጥቄ  ተማሪ የነበረውና ክራርና ከበሮ በመጫወት የተካነው ተመስገን ታረቀኝ፤ ድምፃዊቷ ገነት አሰፋና ሌላው ከበሮ ተጨዋች ሮቤል ተስፋዬ ናቸው፡፡ ከባንዱ ጋር አራት የባህል ተወዛዋጆች የሚሰሩ ሲሆን የጅቡቲና ሌሎች የአፍሪካ አገራት ሙዚቀኞችም አብረዋቸው ይሠራሉ፡፡

ክራር ኮሌክቲቭ ካለፈው አንድ ወር ወዲህ በአፍሪካን ኤክስፕረስ አማካኝነት በዩናይትድ ኪንግደም ስድስት ከተሞች በተዘጋጁ ኮንሰርቶችና ሌሎች የሙዚቃ ዘግጅቶች ላይ ሲሳተፍ  ሰንብቷል፡፡ በአፍሪካን ኤክስፐርስ ቱር ክራር ኮሌክቲቭ ጋር አይማዱክ ማርያም ፋቱማታ ሲያዋራ፣ ቱዋማኒ ዲያቤቴ፣ ቶኒ አለን፣ ኒኮላስጃፒ እና ኪያላላ ግሬጅ ይገኙበታል፡፡

የክራር ኮሌክቲቭን የመጀመሪያ አልበም “ኢትዮጵያ ሱፕር ክራር”ን የገመገመው የጋርዲያን ጋዜጣ ዘገባ ባንዱ የኢትዮጵያ ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎችን፣ (ክራርና ከበሮን) በባህላዊ የአዘፋፈን ቅላፄ ውዝዋዜ በማቅረብ በ2012 ዓለም አቀፍ እውቅናቸው ጨምሯል ክራር ኮሌክቲቭ በአልበማቸው እቴሜቴ፣ እንደ እየሩሳሌምና ትዝታ የተባሉት ዘፈኖችንም ይጥላሉ ብሏል፡፡

ክራር ኮሌክቲቭ የሙዚቃ ባንድ ከመመሥረቱ በፊት ኢትዮጵያውያኑ የሙዚቃ ባለሙያዎች በዲያስፖራ ለሚገኙ ማህበረሰቦች የሠርግ ዘፈን በመጫወት ይታወቁ ነበር፡፡ ባንዱ ከተመሠረተ በኋላ ግን በተለያዩ የአውሮፓ አገራት በተካሄዱ የሙዚቃ ፌስቲቫሎች ላይ ዝግጅቶቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን በለንደን ኦሎምፒክ ወቅትም ስራዎቻቸውን ያቀረቡት መድረክ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

 

 

 

Read 1215 times Last modified on Saturday, 29 September 2012 10:04