በባህል ላይ ያተኮረው እና አዚዶልፕ መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን ያሰራው “ጢባጢቤ” የተሰኘ የዳንስ ድራማ ፊልም ሰኞ እንደሚመረቅ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡ ፊልሙ በ7D እና 5D ካሜራ የተቀረፀ ነው ተብሏል፡፡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ሰኞ ከቀኑ 11 ሰዓት የሚመረቀውን ፊልም ፅፋ ያዘጋጀችው ቅድስት ይልማ ስትሆን አዚዛ አህመድ፣ ሚካኤል ሚሊዮን፣ ሚካኤል ዮሐንስ፣ ዘነቡ ገሠሠ እና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ የፊልሙ ኬርዮግራፈር አዲሱ ደምሴ ነው፡፡