በአንጋፋው ደራሲ ሃያሲና የኢኮኖሚ ባለሙያ አስፋው ዳምጤ የተሰናዳው “የአማረኛ ጥበበ ቃላት ቅኝት” የተሰኘ መፅሐፍ፣ ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡
መፅሐፉ፤ የዘመናት ታሪክን የሚያሳይ፤ የመቶ ዓመት የልብወለድ ታሪኮችን የሚተነትን ነው ተብሏል፡፡
በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ሰዓሊ እሸቱ ጥሩነህ፣ ደራሲና መምህር ደረጀ ገብሬ፣ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ፣ ደራሲ ዘነበ ወላ፣ ደራሲና ሰዓሊ ዳንኤል ታዬ፣ ደራሲና አርታኢ ሁሴን ከድር እንዲሁም ኤርሚያስ ሁሴን ጥበባዊ ሥራዎቻቸውን ለታዳሚ የሚያቀርቡ ሲሆን፤ ይታገሱ ጌትነት ደግሞ መድረኩን ይመራዋል ተብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና