Thursday, 19 October 2023 00:00

የድምፃዊ ብስራት ሱራፌል “ማለፊያ” አልበም ቅዳሜ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የድምፃዊ ብስራት ሱራፌል አዲሱ “ማለፊያ” የተሰኘ የሙዚቃ አልበም  የፊታችን ቅዳሜ፣  ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሸራተን አዲስ  ጋዝላይት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡

 የግጥምና ዜማ ደራሲ እንዲሁም ፕሮዱዩሰር የሆነው ድምፃዊ ብስራት ሱራፌል፣ በቅርቡ ለአድማጭ ያደረሰው  ሁለተኛ የሙዚቃ አልበሙ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነትና ተቀባይነት እንዳገኘ ይነገርለታል፡፡

በርካታ የግጥምና ዜማ ሥራዎችን ለሌሎች ድምጻውያን በመሥራትና በመስጠትም  የሚታወቀው ድምጻዊው፤ እስካሁን ከሰጣቸው መካከልም ድምፃዊት ኩኩ ሰብስቤ፣ ሄለን በርሄ፣ ቬሮኒካ አዳነ፣ ሐይማኖት ግርማ  ይጠቀሳሉ፡፡
 

የ“ማለፊያ” አልበም  የምረቃ ሥነስርዓት፤ ታዋቂ ድምጻውያን፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎችና  ታዋቂ ግለሰቦች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው  የአርቲስቱ አድናቂዎች በተገኙበት ይከናወናል ተብሏል፡፡

Read 1342 times