• በ4 ወራት ውስጥ ከ15 ሺ በላይ ቤት ፈላጊዎችን መዝግቧል
በአራት ወራት ውስጥ 15 ሺህ 388 ቤት ፈላጊዎችን መመዝገቡን ያስታወቀው ኪ ሀውሲንግ ፋይናንስ ሶልሽን፤ በዛሬው ዕለት ከ6 ሰዓት ጀምሮ በዲ ሊኦፖል ሆቴል ባካሄደው ዕጣ የማውጣት ሥነሥርዓት 60 ቤት ፈላጊዎችን የቤት ባለቤት አድርጓል፡፡
በዕጣ ከወጡት 60 አፓርተመንት ቤቶች ውስጥ ሰላሳው ባለ ሦስት መኝታ ክፍል፣ ሃያ አንዱ ባለሁለት መኝታ ክፍል ሲሆኑ፤ ዘጠኙ ደግሞ ደግሞ ባለ አንድ መኝታ ክፍል መሆናቸው ተነግሯል፡፡
ዕጣ የወጣላቸው አፓርትመንቶች በፒያሳ፣ በጋርመንትና በሀያት የሚገኙ ሲሆኑ፤ ሙሉ ለሙሉ ግንባታቸዉ ያለቀላቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ኪ ሀውሲንግ፤ በአስር አመት ውስጥ እስከ 100 ሺህ የሚደርሱ ቤቶችን ገንብቶ ለቤት ፈላጊዎች ለማስረከብ ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ባለፈው ነሀሴ ወር የመኖሪያ ቤት ፈላጊዎች በ77 ሺ 280 ብር ቅድመ ቁጠባ የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ሞዴል ፕሮጀክት ማስተዋወቁ አይዘነጋም፡፡
Published in
ዜና