Monday, 22 January 2024 13:01

በአዲስ አበባ "ንባብ እና አገር" የተሰኘ የንባብ ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በአዲስ አበባ "ንባብ እና አገር" የተሰኘ የንባብ ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው

የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ "ንባብና አገር" የተሰኘ የንባብ ፌስቲቫል ከጥር 16 እስከ 23ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
የባህልና ቱሪዝም ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ አስፋው ኩማ እንዳሉት፤ የንባብ ፌስቲቫሉ ዓላማ የከተማው ማህበረሰብን የንባብ ባህል ለማሻሻልና ግንዛቤ ለመስጠት ነው።
ባለፉት ሶስት ዓመታት የተለያዩ በራሪ ጽሁፎች በማዘጋጀት የስርፀት ሥራ ሲሠራ መቆየቱን የገለፁት ሃላፊው፤ በዚሁ ዝግጅት በህትመት ታሪክ ውስጥ በርካታ አስተዋፅኦ ያደረጉ ድርጅቶችና ደራሲያን ታሪካቸው ይወሳል ብለዋል።
የንባብ ፌስቲቫሉ ለ8ኛ ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን ዝግጅቱ በአዲስ አበባ ሙዚየም ይደረጋል።

Read 759 times