Saturday, 24 February 2024 20:26

ሽታዬ ስዊት ሆቴል የአድዋ ድል በዓል ዕለት ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአዲስ አበባ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊት ለፊት የተገነባው ባለ 15 ፎቅ ዓለማቀፍ ሆቴል፤ የፊታችን ቅዳሜ  የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡
ለግንባታ 7 ዓመት የፈጀውና የኩራዝ ወንዝ ኃ.የተ.የግ. ድርጅት አጠቃላይ ፕሮጀክት አንደኛው እህት ኩባንያው ነው የተባለው ሽታዬ ስዊት ሆቴል፤ አባት አርበኞች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናትና አምባሳደሮች በተገኙበት ይመረቃል ነው የተባለው፡፡
በ600 ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈው ሆቴሉ G†15 ከአንድ ቤዝመንት ጋር ያለው ሲሆን፤ በቂ የመኪና ማቆምያ ቦታም ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ሆቴሉ የራሳቸው ማብሰያ ክፍሎች ያላቸው ሰፋፊ ምቹና ዘመኑ ያፈራቸውን መገልገያዎች የያዙ መኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ ለየት የሚያደርገውም የፔንት ሃውስ ክፍል ምርጫ ያለው ነው ተብሏል፡፡
የባህል ምግብ አዳራሽ፣ የመዋኛ ሥፍራና የሰርግ ስብሰባ አዳራሾች ያካተተው ሽታዬ ስዊት ሆቴል፤ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተነግሯል፡፡
በሆቴሉ የምረቃ ሥነስርዓት  ላይ ለአባት አርበኞች ምስጋናና ዕውቅና እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡

Read 445 times