Friday, 15 March 2024 11:32

የ“ሕግ እና ሰብዓዊነት” መጽሐፍ ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ሀገራችን በፖለቲካ፡ ኢኮኖሚና ማሕበራዊ ዘርፎች የገጠሟትን ተግዳሮቶች በመንቀስና ለችግሮችም የመፍትሔ ሀሳቦችን የያዙ በርካታ መጣጥፎችን ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጦች በማበርከት የሚታወቁት ዶ/ር ታዬ ብርሃኑ፤ "ሕግ እና ሰብአዊነት" የተሰኘ  መጽሐፋቸውን ለሕትመት ብርሃን አብቅተዋል።
መጽሐፉ አሁን ያለንበትን ሀገራዊ ምስቅልቅል የወለደውን የኢፌዲሪ ሕገመንግሥትን በብርቱ የሚሄስ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ከገባንበት ፖለቲካዊ ቅርቃር ለመውጣት ፣ሥርነቀላዊ መዋቅራዊ ማሻሺያ ማምጣት የሚቻልበትን የመፍትሔ ሐሳብም ያመላክታል።
 "ሕግ እና ሰብአዊነት"  በ7 ምዕራፎች ተከፋፍሎ፣ በ234 ገጾች የተቀነበበ ሲሆን፤ በ300 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ መጽሐፉን ጃፋር የመጻሕፍት መደብር እንደሚያከፋፍለውም ታውቋል፡፡

Read 877 times